-
በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት ያለ ዐደራ
(1 ጢሞቴዎስ 6:12-16) በጣም ብዙ እያሰብኩበት ያለ ጉዳይ፤ ደግሞ ለረጅም ጊዜ የምጸልይበት ርዕሰ-ጉዳይ፤ ቤተክርስቲያን እና አማኞች የአስተርዕዮ ተርካቢዎች (መገለጥ) እና ባለአደራዎች መሆናችንን እንድንረዳ ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ሕዝብ አስተርዕዮ የቀረጸው ሕዝብ እንደሆነ ሁሉ ይህንንም መገለጥ ለመጪው ትውልድ አስተላላፊ አካል ነው። በመከራ፤ በሥደት፤ በጅራፍ የጎረባበጠው ሰውነቱ እና በወህኒ እስር እንዲሁም በብርድ ስቅይት ያለው ሽማግሌው ጳውሎስ፤ ለሊት እንቅልፍ የነሳው ጉዳይ የእግዚአብሔር ሕዝብ እና ተተኪ መሪዎች ይህን አደራ ተረድተውት ይሆን? የተቀበሉትንስ እንደተቀበሉትስ ያስተላልፉት ይሆን? የሚል ይመስላል። [su_pullquote]”መልካሙን የእምነት ገድል ተጋደል፥ የተጠራህለትንም በብዙም ምስክሮች ፊት በመልካም መታመን የታመንህለትን የዘላለምን ሕይወት ያዝ። ሁሉን በሕይወት በሚጠብቅ በእግዚአብሔር ፊት፥ በጴንጤናዊውም በጲላጦስ ዘንድ መልካሙን መታመን በመሰከረ በክርስቶስ ኢየሱስ ፊት አዝሃለሁ፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስኪገለጥ ድረስ ያለ እድፍና…
-
የክብር ጎዳና፡ (መስቀልና ዙፋን – ክፍል 2)
ክርስቶስና የመስቀሉ ተልዕኮ መውረድ እና መውጣት በዮሐንስ ወንጌል ❝ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ «ሰዓቱ ደርሶአል»፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው…እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ❞ ❝ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “የሰው ልጅ የሚከብርበት «ሰዓቱ ደርሶአል»፤ እውነት እላችኋለሁ፤ የስንዴ ቅንጣት መሬት ላይ ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች… “አሁንስ ነፍሴ ተጨነቀች፤ ምን ልበል? አባት ሆይ፤ ከዚች ሰዓት ታድነኝ? የለም፤ ይሁን የመጣሁት ለዚህች ሰዓት ነውና። አባት ሆይ፤ ስምህን አክብረው❞ የዚህ ጽሑፍ አጠቃላይ ሐሳብ በዮሐንስ ነገረ-መለኮታዊ አስተምህሮ ውስጥ ለይትና…
-
መስቀልና ዙፋንን ያማጠንች ቤተክርስቲያን (መስቀልና ዙፋን – ክፍል 1)
ክራር-ነክ ሙዚቃ መሳሪያዎች በየጊዜው መቃኘት አለባቸው። እያንዳንዱ ክር ትክክለኛ ቅኝቱን እስኪይዝ ድረስ በሁለት ጥግ ተወጥሮ ይቃኛል። የረገበ ክር ዜማ አይደረድርም። አንዷ ክር በግማሽ ወይም በሙሉ ኖታ እንኳ ወጣ ወይ ወረድ ብትል፤ የዜማ መርህ ስለሚጣረስ ጥዑም ቅኔን መደርደር አይችልም። ስለዚህ ተጨዋቹ መሳሪያውን መቃኘት አሊያም ቅኝት የሚያውቅ ሰው ጋር በመውሰድ ማስቃኘት ይኖርበታል። ቅኝታችን ታድያ ምን ይመስላል? ልክ እንዲሁ ከላይ በሰፊው እንዳተትን፤ ወንጌላችን በክርስቶስ መምጣትና ዳግም መምጣት ተወጥሮ በትክክል የተቃኘ ቃል ነው። ከዚህ “ውጥረት/tension” የተነሳ “መዳናችን፤ ተስፋችን፤ ልጅነታችን፤ በረከታችን፤ አላማችን፤ ቅድስናችን..ወዘተ…” ልክ እንደ እያንዳንዱ የክራር ክሮች “በክርስቶስ መምጣትና ዳግም ምጻት” ቅኝት ይዘዋል (inaugurated eschatology)። ክርስቶስ ከሰማያዊ ሥፍራ (በአባቱ ቀኝ) ሆኖ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት፤ በዓለም ዙሪያ ላሉ ህዝቦችና በአየሩ ላይ ላሉ አለቆች ይህ ብዙ…
-
ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ
❝የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ። ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን? እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል። መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት፥ ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም። መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል። ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ❞ (ማቴ. 7:15–20) ❝Προσέχετε ἀπὸ τῶν ψευδοπροφητῶν, οἵτινες ἔρχονται πρὸς ὑμᾶς ἐν ἐνδύμασιν προβάτων, ἔσωθεν δέ εἰσιν λύκοι ἅρπαγες. ἀπὸ τῶν καρπῶν αὐτῶν ἐπιγνώσεσθε αὐτούς.❞ የምንባቡ መዋቅራዊ ዓውድ (Structural Context of the Passage) የማቴዎስ ወንጌል “በትረካ-ንግግር” የተዋቀረ መጽሐፍ ነው።[1] ለምሳሌ ያህል፦ (ትርካ) – ከማቴ. 1 – 4: የክርስቶስ ትውልድ፤ ልደትና አገልግሎት (ንግግር) – ከማቴ. 5 –…
-
አስተርዕዮተ-እግዚአብሔርና ሰው
እውነተኛ ክርስትያናዊ አስተምህሮ (በምንም አይነት ጉዳይ ላይ ያተኮረ) የእግዚአብሔርን መገለጥ ማዕከል ያደረገ መሆን አለበት። ከዚህ የተነሳ ማንኛውም ትምህርት ይሁን ስብከት፤ መዝሙር ይሁን ስግደት፤ እንዲሁም አምላክ ተኮር የሆነ ማንኛውም ንግግር/ ጹሑፍ፤ እግዚአብሔርን ያጎላል ወይም ያማክላል፤ አሊያ ያንኳስሰዋል ወይም ያደበዝዘዋል። ይህ የማይመለከተው አማኝ የለም። ያህዌህ ኢዮብን “ዕውቀት በጐደለው ቃል፣ ዕቅዴን የሚያጨልም ይህ ማን ነው?”(ኢዮ. 38:2) ብሎ እንደገሰጸው አንዳንድ ጊዜ ንግግራችን ከእግዚአብሔር ማንነት ጋር የሚጋጭ፤ ክብሩን የሚያደበዝዝና የመገለጡን ብርሃን የሚያጨላልም ይሆንብናል። ማስተዋልን ገንዘቡ ያላደረገ ንግግር በመሆኑም በሰሚው ልቡና ውስጥ አብርሆት ሰጪ አይሆንም። በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ትምህርተ-ሰብዕ (ሰው) እግዚአብሔርን ማዕከል ያደረገ ትምህርት ነው ስለ አስተርዕዮተ-እግዚአብሔር (ስለ እግዚአብሔር መገለጥ) ስንነጋገር ልናገናዝብ የሚገቡ ሁለት መሠረታዊ ገጽታዎች አሉት። ወይም መገለጡን ከሁለት ገጽታዎች አንጻር መመልከት ይገባናል። በአንደኛ ደረጃ…
-
Workshop 01: The Relationship between Biblical Authority & Worldview Contextualization
This is a 3-part workshop designed to introduce the basic tools necessary to understand and apply scripture to our lives. The bible reflects the character and person of God, as such it shapes our faith/doctrine as well as our practice/ethics. We shall answer questions such as how to discover the meaning of a given biblical text, how to perform sound exegesis and basic discourse analysis as well as create discourse outlines. Moreover, several pitfalls in understanding the message of scripture originates from what I call “flat-reading.” That is a way of reading the bible that does not account for its multi-faceted genre: historical narrative, poetry, law, gospel, letter, apocalyptic writing,…
-
የይሁዳ መልክት – መንደርደሪያ ነጥቦች
[su_note note_color=”#f4f4f3″]► QUESTION: ሳሚየ እቺ እስቲ ኣስረዳኝ- “ከረጅም ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንድ ሰዎች ሾልከው ወደ እናንተ ገብተዋልና፤ እነርሱ ፈሪሀ እግዚአብሔር የሌላቸው፣ የአምላካችንን ጸጋ በርኵሰት የሚለውጡና እርሱ ብቻ ልዑል ገዣችንና ጌታችን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የሚክዱ ናቸው” ይሁዳ 4 “ምን ማለት ነዉ ከረጅም ጊዜ በፊት ለዙህ ፍርድ የተጻፉ ሲል? ጸጋ ብርኩሰት መለወጥስ? የጌታ የሱስ ጌትነት መካድ እንዴት ነዉ?” (Azeb Berhane)[/su_note] መግቢያ “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። ከብዙ ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ገብተዋልና፤ ኃጢአተኞች ሆነው የአምላካችንን ጸጋ በሴሰኝነት ይለውጣሉ ንጉሣችንንና ጌታችንንም ብቻውን ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ” የይሁዳ መጽሐፍ ይዘት በሦስት…
-
የሕዝቅኤል ትንቢትና ቅዱሳት መጻሕፍት
በእያንዳንዱ ትውልድ መቼም መጪና ሂያጅ፤ እንዲሁም ወቅታዊና ጊዜያዊ፤ የሆኑ አያሌ ጉዳዮች አሉ። በአንድ ወቅት መሠረት አድርገን የያዝነው በሌላ ደግሞ "አይ እርሱማ አሁን አይሰራም" እንባላለን። በዚህ በሕዝቅኤል መጽሐፍ ጥናት ክፍላችን ላይ ያተኮርነው - "ስለ ሕዝቅኤል መጽሐፍ፤ ከቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ጋር፤ ልናውቅ በሚገባን እና ዘመን መጠቅ በሆኑ በአራት የቅዱሳት መጻህፍት ባህርያት ላይ ነው" እነዚህ በተለይ በዘመናችን ቤተክርስቲያን ትኩረት ልትሰጣቸው የሚገቡ መሠረቶች ናቸው። እነዚህ ከብዙ የአጠናንና የአስተምህሮት ችግሮች እንድንጠበቅ ከመርዳታቸው ባሻገር፦(1) ቤተክርስቲያን በቃሉ ላይ ትኩረት እንድታደርግ፤ ቃሉንም ስታስተምር በጥራት እንድታስተምር ይረዳታል ብዬ አምናለሁ። (2) ቤተክርስቲያንን የመጽሐፍ ቅዱስ ስልጣኑን፤ በነጠላ በቂነቱን፤ ግልጽነቱን እና እግዚአብሔርን ለመምሰልና የእ/ር ሰው ለመልካም ሥራ ሁሉ ዝግጁ እንዲህን የሕይወት-ሞት-አስፈላጊነቱን እንድታስተውል ያደርጓታል።(3) ቤተክርስቲያን ክርስቶስን ማዕከል ባደረገ አስተምህሮትና አምልኮት እንድትመሰረት ይረዷታል።(4) ከነፍስ…
-
የሕዝቅኤል መጽሐፍ ጥናት: የእግዚአብሔርን ክብር ማወቅ
ዕለቱ July 31, 593 ቅ.ዓ. ነው። ምናልባትም ሕዝቅኤል በእግዚአብሔር ፊት ልቡን ለማፍሰስ ወደ ኮቦር ወንዝ ዳር ሔዶ ሊሆን ይችላል። ይህም ይሆን ይህ የምናውቀው ነገር ቢኖር ሕዝቅኤል ካህን ወይም የካህን ልጅ እንደነበር እና ይህ ቀን ደግሞ የካህኑ 30ኛ የልደት ዓመቱ እንደሆን ነው። የካህኑ የቡዝ ልጅ እንደመሆኑ እድሜ ልኩን ለካህንነት ሲገዘጋጅ እንደ ኖረ መገመት አዳጋች አይደለም። ሆኖም ግን ከዓምስት ዓመታት በፊት በ597 ቅ.ዓ. ናቡከደነጾር ሁለተኛውን ምርኮ ባደረገ ጊዜ የይሁዳን ንጉሥ ዮአኪንንና ከእርሱ ጋር ወደ 10ሺህ የሚጠጉ የንጉስ ቤተሰቦችንና ሹሟሙንቶችን ተማርከው ወደ ባቢሎንት ተጓዙ። ከነዚህ መካከል የ25 ዓመት ወጣት የሆነው ሕዝቅኤል ነበረበት። ይህ ቀን ኢየሩሳሌም ቢሆን ኖሮ ሰላሳኛውን ዓመት የሚያከብርበት ቀንና ወደ ክህንነት አገልግሎቱ የሚካንበት የሹመት ቀን ይሆን ነበር። አሁን ግን በውርደት ከኢየሩሳሌም…
-
The Book of Hebrews: the author, the audience and the book
[su_youtube url=”https://www.youtube.com/watch?v=_OqnYyJwO10″] [su_youtube url=”https://www.youtube.com/watch?v=0qUZDI8LIq4″] More on Hebrews [pt_view id=”12e82f1c0e”]
-
I Counsel You to Buy Gold from Me Refined by Fire: So that You may be Rich!
If you grew up in one of the metropolitan city of Ethiopia, you have encountered street vendors. Alas, their persuasion, for you to buy their products, was almost a nag. Before you get from point A to point B, they would interrupt you several times yelling, “Sir. come here, Ma’am, buy this…”. Likewise, here in New York city, you cannot cross 47th street between fifth and sixth avenue without encountering a mob of jewelry sales persons. It is more likely that Isaiah employs the voice of a street vendor, metaphorically, here in our text. Isaiah resembles Yahweh’s plea to that of street vendors (as we shall see Jesus also alludes…
-
ክርስቶስን ማዕከል በማድረግ፤ በኪዳን የተመረቀ መንግሥት (Kingdom through Covenant, climaxing In Christ)
የአባቶቻችን አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅና የያዕቆብ አምላክ ብላቴናውን ኢየሱስን አከበረው፤ እናንተ ግን እንዲሞት አሳልፋችሁ ሰጣችሁት፤ ጲላጦስ ሊፈታው ቢፈልግም እናንተ በእርሱ ፊት ካዳችሁት፤ 14ቅዱሱንና ጻድቁን ክዳችሁ ነፍሰ ገዳዩ እንዲፈታላችሁ ለመናችሁ፤ የሕይወት መገኛ የሆነውን ገደላችሁት፤ እግዚአብሔር ግን ከሙታን አስነሣው፤ እኛም ለዚህ ምስክሮች ነን። ይህ የምታዩትና የምታውቁት ሰው የበረታው በኢየሱስ ስም በማመን ነው፤ ሁላችሁም እንደምታዩት ፍጹም ፈውስ እንዲያገኝ ያደረገው የኢየሱስ ስምና በእርሱ አማካይነት የሚገኘው እምነት ነው። “አሁንም ወንድሞች ሆይ፤ እናንተ ይህን ያደረጋችሁት እንደ አለቆቻችሁ ሁሉ ባለማወቅ እንደሆነ ዐውቃለሁ። እግዚአብሔር ግን የእርሱ የሆነው ክርስቶስ መከራን እንዲቀበል አስቀድሞ በነቢያቱ ሁሉ አፍ የተናገረውን ፈጽሞአል። እንግዲህ ኀጢአታችሁ እንዲደመሰስ ንስሓ ግቡ፤ ከመንገዳችሁም ተመለሱ፤ ከጌታም ዘንድ የመታደስ ዘመን ይመጣላችኋል፤ 20ደግሞም አስቀድሞ ለእናንተ የተመደበውን ክርስቶስን እርሱም ኢየሱስን ይልክላችኋል። እግዚአብሔር አስቀድሞ በቅዱሳን…
-
Two-sets of words that every christian should know
There are two important set of words concerning God and his relationship with us that will both enrich our understanding as well as help us keep away from contradictions and wrong notions about God. These are: “Transcendence-Immanence” and “Creator-Creature” distinctions. These two words provide us biblical balance in our knowledge of God and His ways. Those of you who follow this blog-posts know these pretty well. Therefore, I write as a conversation than formal post. TRANSCENDENCE-IMMANENCE DISTINCTIONS Transcendence underlines the reality that God is God and he’s not us. Whereas God’s immanence underscores the fact that, this God who surpasses all understanding (i.e. Transcendence), stooped down and revealed Himself to…
-
▶ ወንጌል ስለ ልጁ ሹመት የምሥራች ቃል ነው፡- በሰማይና በምድር ኢየሱስ ጌታና ክርስቶስ ሆኖ ተሹሟል
“ወንጌሉም ስለ ልጁ፣ በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ሆነ፣ በቅድስና መንፈስ ደግሞ ከሙታን በመነሣቱ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ በኀይል ስለ ተገለጠው ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው” 1:3-4 ይህ የምንናገርለት ወንጌል ባለቤትና ይዘት ዓለው። ወንጌል የእግዚአብሔር ነው “ለእግዚአብሔር ወንጌል የተለየ…” (1:1)። ወንጌል ባለቤት፤ ምንጭና ይዘት ስላለው የአንድ ተቋም ይዞታ አይደለም፤ ባለቤቱም እግዚአብሔር አብ ነው! ከዚህ የተነሳ ይህንን ወንጌል ማንም ሥጋ ለባሽ “የእኔ ነው” ሊለው አይችልም። እንደዚሁም ወንጌል “ባለቤት” ብቻ ሳይሆን፤ “ይዘትም” አለው! ይዘቱ ደግሞ አንድያ ልጁ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው! “በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ሆነ…ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው”። ይህ ይዘት በሌላ ነገር ሊተካ በፍጹም አይቻልም። ይዘቱ የተቀያየጠ ወንጌል፤ በገላትያ መጽሐፍ መሠረት፤ እንግዳ ወንጌል ነው። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ይዘቱ ያላደረገ ወንጌል፤ የሚሰብክ…
-
I AM WHO I AM: Appropriate and Inappropriate Languages about God and Christ
Earlier generations of Christians used to put a lot of effort to discern and talk about the nature of what it is that they believe. That is to say, for them, knowing “what it is” that they believe precedes from what it is they are to “practice and experience.” Worship is Learning the Language of God’s self-Revelation. Worship is only possible, when we begin to learn to speak the language of scripture, the language of God, the language of Yahweh’s self-revelation in Christ Jesus. Everything else is anywhere between defective and idolatrous. I am fluent in Amharic. The language is natural for me. I learned to speak it first and…