-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-2)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) ባለፈው ክፍል፣ እግዚአብሔርን መግለጥ የሚችለው «ራሱ እግዚአብሔር ብቻ» እንደሆን ተመልክተናል። ስለዚህም ያለ አስተርዮ እግዚአብሔርን ማወቅ አንችልም። ስለ ነገረ-አስተርዕዮም (እግዚአብሔር ራሱን እንዴት እንደገለጠ) በቂ ግንዛቤ ካልያዝን ስለ እግዚአብሔር ያለን ግንዛቤ ሊዛባ ይችላል። ሁለቱ የተያያዙ ናቸው። ለምሳሌ በማርቲን ሉተር አስተሳሰብ ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበረው ነገር፦ እግዚአብሔር “ዴዩስ አብስኮንዲቱስ\deus absconditus\ የተሰውረ-አምላክ” እንዲሁም “ዴዩስ ረቨላቱስ\deus revelatus\የተገለጠ-አምላክ” መሆኑ ነበር (“the hidden God” and “the revealed God”)። ለሉተር ሰው ያለ አስተርእዮ የእግዚአብሔርን ማንነት ይሁን ዘላለማዊ ፈቃዱን ማወቅ አይችልም። በተጨማሪም፤ ለሉተር ይህ የተስተረዓየው የእግዚአብሔር ክብር በክርስቶስ መስቀል ውስጥ ተሰውሯል። ተገልጧል-ግን-ተሰውሯል። የተሰወረው በመስቀሉ በኩል ሊያገኙት ለማይፈልጉት ነው። ለዚህ ነው ሉተር “የመስቀል…
-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-1)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) “እግዚአብሔር ማን ነው?” ለሚለው ጥያቄ በቂ ያልሆነ ወይም የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖረን ከሚያደርጉን ነገሮች አንዱና ተቀዳሚው፤ ስለ ነገረ-አስተርዮ በቂ ያልሆነ ግንዛቤ መጨበጥ ነው። ለምን!? ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ማወቅ የምንችለው «እግዚአብሔር ራሱን የገለጠልን እንደሆነ» ብቻ ስለሆነ ነው። እግዚአብሔርንም መግለጥ የሚችለው ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህም ያለ አስተርዮ እግዚአብሔርን ማወቅ አንችልም። በግሌ ሕይወት ይሁን በሌሎች የተመለከትሁት አንድ ነገር ቢኖር «ስለ እግዚአብሔር የተዛባ አመለካከት ምንጩ የተዛባ ነገረ-አስተርዕዮ» መሆኑን ነው። ስለዚህ አስተርዕዮ ምንድር ነው? አስተርዕዮ የእግዚአብሔር ማንነትና የዘላለም ፈቃዱ መገለጥ ነው። የነገረ-አስተርዮም ቁልፍ መልክት “እግዚአብሔር ሕያው ሕላዌ\ a Personal Being” መሆኑ ነው። ይህ አምላክ «“እኔ” እያለ ስለራሱ፣ ይግባባው ዘንድ…
-
ነገረ-ክርስቶስ በዕብራውያን መልዕክት: መቅድም
(The Christology of Hebrews: An Introduction) የእብራውያን መጽሐፍ የሹመት መጽሐፍ ነው። የመጽሐፉን ሙሉ ነገረ–መለኮታዊ ክብደት የሚሸከመው «በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ» የሚለው እውነታ ነው (ዕብ 1:3; 1:13; 8:1; 10:12-13; 12:2)። ኢየሱስ ከሁሉ እንደሚልቅ ሰባኪያችን ሲሞግት (ጸሐፊውን የምጠራው ሰባኪው በማለት ነው) የሚያቀርባቸው መሠረታዊ ማስረጃዎች በሙሉ በዚህ ልዕልና እና እውነታ ላይ የተመረኮዙ እንዲሁም የተቃኙ ናቸው። እውነታው «ተቀመጠ» (ኧካቲሰን | ἐκάθισεν)” (1:3) የሚለው ሲሆን፤ ልዕልናው ደግሞ የተቀመጠበት ምጡቅ ሥፍራው ነው “በሰማያት በግርማው ቀኝ”። ስለዚህ የሰባኪው ማዕከላዊ መልዕክት <ኢየሱስ ይልቃል! ምክኒያቱም ኢየሱስ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀምጧልና> የሚል ነው። ይህንን ልዕልና ከእብራውያን የነገረ–መለኮታዊ አቀራረብ ስልት አንጻር በሁለት ንጽጽራት መድበን መመልከት እንችላለን። አንደኛው ምድራዊ–ሰማያዊ የሚል ‘የቁም ንጽጽር’ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ይኸኛውና ወዲያኛው ዓለም የሚል ‘ሰያፍ ንጽጽር’ ነው።…
-
ስለ አፈታት ጥቂት፡ ከምንባቡ ይዘት ጋር በቅርበት መተዋወቅ
ለአንዳንዶች ይጠቅም ስለሚችል፤ በአንድ ምንባብ ላይ ያተኮረ ትምህርት/ስብከት ሳዘጋጅ ወይም ጽሑፋዊ ሐቲት ስጽፍ፣ ጽሑፋዊ ዓውዱን ለማግኘት የምከተለው ቅደም ተከተል ከሞላጎደል በጥቂቱ እነሆኝ። መጠነኛ የቋንቋ ስልጠና ለወሰዱ ደግሞ አንዳንድ ይጠቅማሉ ብዬ ያሰብኳቸውን መርጃ መጻሕፍቶችንም እጠቁማለሁ ።ከዚህ ቀጥሎ የማሰፍረው በተከታታይ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለ ምንባብ አተታተት የማቀርበው ይሆናል። የሚከተለው የመጀመሪያው መርህ ነው። #አንደኛ፡ ከምንባቡ ይዘት ጋር በቅርበት መተዋወቅ ወፍ በረር ትውውቅ (Big Picture Reading) የምንባቡን ወሰን ማወቅ። «ምንባባችን የት ጀምሮ የት ያበቃል?» የሚለውን ጥያቄ ይመልሳል። አማርኛ አንባቢዎች የምንባባችንን አወቃቀር (outline) ወደ ሦስት የሚጠጉ ማጥኛ ጽሑፎችን (Study Bibles) ወይም ማብራሪያዎችን ማወዳደር ተገቢ ነው። መጠነኛ የቋንቋ ስልጠና ለወሰዱ ደግሞ ንባባዊ-ትንታኔ የሚያደርጉ (Discourse Analysis) ሥራዎችን ማመሳከር ይገባል። ለምሳሌ 1 ቆሮ. 1፡23 ስናጠና የምንባባችን ዋና ክፍል…
-
የተሾመው መልከ ጼዴቃዊው ካህንና ንጉስ፡ የእብራውያን መጽሐፍ ዳሰሳ
-
ከትንሳኤ ማግስት፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መንፈሳዊነት
ቤተክርስቲያን ስላለችበት ሁኔታ እንዲሁም በውስጧ እየሆኑ ስለሉት ስብራቶችና ግራ የሚያጋቡ ነገሮች ስታስቡ “ኧረ መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚል ጥያቄ አይፈጠርባችሁም? ክርስቶስ የሞተውና የተነሳው “ለዚህ ነው?” አያስብላችሁም? ወይም ይህንን ጥያቄ እንደገና አንስተን እንደገና መመለስ እንዳለብን የዘነጋነው የቤት ሥራ አይመስላችሁም? ስለ ችግሩ እየተወያየንና አስተያየቶቻችንም እየቸርን የቤት-ሥራችን ግን ተቆለለ አይደል? እኔ ተቆልሎብኛል። ልክ የትዳር ሕይወት ከሠርግ ማግስት እንዲጀምር መጽሐፍ ቅዱሳዊውም “እውነተኛ ሕይወት” [ያ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ እየደጋገመ እንደ አዝማች ያሳሰበው ጉዳይ] እንዲሁ ከትንሳኤ ማግስት ይመስለኛል። መቼም ሞቱንና ትንሳኤውን አክብረን ስናበቃ ራሳችንን ማሳሰብ ያለብን ብዙ ነገሮች እንዳሉን ይሰማኛል። ከእነዚህ አንዱና ዋነኛ ግን “መንፈሳዊነት ምን ማለት ነው?” የሚለው መሆን አለበት። ይህ ወቅት ሞቱንና ትንሳኤውን ይዘን ሳናሰልስ ወደ ሥራ የምንሔድበት እንጂ፤ ወደ ሌላ ርእሰ-ጉዳይ የምንሸጋገርበት እንዳልሆነ ሁላችንም…
-
መስቀልና ኪዳን፡ የመጨረሻው እራት
[su_quote]እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ [16] እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው (ሉቃስ 22:15-16)[/su_quote] ይህ እራት እጅግ የከበረ እራት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር ❝ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤ [ግን] ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና❞ ይህ የሚያሳየን ይህ የመጨረሻው እራት ሥርዓት ብቻ ሳይሆን፣ በመረዳትና ተገቢ በሆነ መንገድ የምንቋደሰው፣ ሕይወትና ሞት ያለበት እራት መሆኑን ነው። ይህ እራት በማቴ. ማር. እና ሉቃ. ላይ “የፋሲካ እራት” ሲሆን በዮሐንስ ወንጌል ላይ ደግሞ በተጨማሪ “የስንብትም” እራት ነው። ልክ ይስሐቅ ለልጁ ኤሳው “ሳልሞት ነፍሴ እንድትባርክህ… አዘጋጅተህ እበላ ዘንድ አምጣልኝ” (ዘፍ 27:4) እንዳለው ማዕድ በጥንታዊው ዓለም “የስንብት” ሥርዓትም ጭምር ነበር። ሙሴ ህዝቡን ተለይቶ ሲሔድ…
-
መስቀልና ኪዳን፡ የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው
“በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤ ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው። ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤ ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፥ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ። እንግዲህ ከዚያ ቀን ጀምረው ሊገድሉት ተማከሩ።” (ዮሐ.11:49–53) የክርስቶስ መስቀል ምን ሥራ ሠራ? ክርስቶስ ከመወለዱ ጀምሮ እስከ መከራው፣ ከሞት ትንሳኤው እስከ እርገቱ፣ እንዲሁም በሰው እጅ ወዳልተሰራችው ቤተ-መቅደስ እስከመግባቱ እና በአብ ቀኝ እስከመቀመጡ ድረስ ምን ተከናወነ ብለን ብንጠይቅ አያሌ ነገሮችን መዘርዘር እንችላለን። ሆኖም ግን ይህንን ሁሉ በአንድ ቃል ብናጠቃልል፤ ክርስቶስ በማንነቱ እና በቃሉ፣ በተለይ በመስቀል ሞቱና…
-
የተሰቀለ-ክርስቶስ
ዛሬ እንደ ግሪጎሪያን አቆጣጠር የክርስቶስ የስቅለት ቀን ነው። በዚህ ቀን አንድ ጸሎት አለኝ “የዚህ ቀን እውነታ ሳያቋርጥ በዘመናችን እና በትውልዳችን እንዲቀጥል…ክርስቶስ እንደተሰቀለ ሆኖ በመልዕክታችን እንዲኖር! (ገላ 3:1 |፡1 ቆሮ. 2:2-3)” ኢየሱስን እንደ ክርስቶስ መቀበል እና እንደ ተሰቀለ-ክርስቶስ መቀበል ይለያያሉ። እኛ የምንሰብከው “የክርስቶስ መስቀል” ከሌሎች መስቀሎች ልዩ ያደረገው፤ “መሰቀል” የሚባለው እውነታ ሳይሆን (በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አይሁድ ወጣቶች ተሰቅለው ነበር – በተለይ በ4BC አካባቢ ላይ)፤ በመስቀሉ ላይ የተሰቀለው እርሱ «ማን መሆኑ ነው»። ይህ የምንናገርለት መስቀል “የክርስቶስ መስቀል” ነው። በሰው አስተሳሰብ ሁለቱ ቃሎች፡ “ክርስቶስ” እና “መስቀል” አብረው የማይቀመጡ ቃሎች ናቸው። ኢየሱስ አስቀድሞ መከራን እንደሚቀበልና እንደሚገደል ሲናገር ጴጥሮስ አይሁንብህ እያለ “ይገስጸው ጀምር” ይለናል። ኢየሱስም “የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው” ምክኒያቱም “አንተ ክርስቶስ…
-
የብሉይ ነቢያት ጥሪ፣ መልክዕክት እና መጻሕፍት
ይህ ትምህርት ከጥቂት ወራት በፊት “የነቢያት ጥሪ፤ መልዕክት እና መጻሕፍት” በሚል ርዕስ ስለ ብሉይ ትንቢት መጻሕፍት ወደ 4.5 ሰዓት የፈጀ ትምህርት ለዴንቨር የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት LIVE ያስተማርሁት ነበር። አስቀድሜ ይህንን ትምህርት እንዳስተምር የጋበዘኝን ፓስተር ኤርሚያስ አማኑኤልን ከልብ እያመሰገንሁ ሌሎችም ትምህርቱን ማዳመጥ እንዲችሉ በማሰብ እንደገና ተቀድቶ፤ አሁን ከጥናት ጹሑፍ ጋር በአንድ ላይ ተቀናብሯል። ❝እንግዲያስ ትንቢታዊው ቃል ይበልጥ ተረጋግጦልናል፤ ሌሊቱ እስኪነጋና የንጋት ኮከብ በልባችሁ እስኪበራ ድረስ፣ በጨለማ ስፍራ ለሚበራ መብራት ጥንቃቄ እንደሚደረግ እናንተም ለዚህ ቃል ብትጠነቀቁ መልካም ታደርጋላችሁ። ከሁሉ አስቀድሞ ይህን ልታውቁ ይገባችኋል፤ በመጽሐፍ ያለው የትንቢት ቃል ሁሉ ማንም ሰው በገዛ ራሱ መንገድ የሚተረጒመው አይደለም፤ ምክንያቱም ትንቢት ከእግዚአብሔር የተላኩ ሰዎች በመንፈስ ቅዱስ ተመርተው ተናገሩት እንጂ ከቶ በሰው ፈቃድ…
-
THE IRREDUCIBLE COMPLEXITY OF THE GOSPEL
Of course that phrase, irreducible complexity, was first coined by a biochemical researcher Michael Behe. He argued that significant biological systems, at their basic form, is “composed of several interacting parts, and where the removal of any one of the parts causes the system to cease functioning (Behe, 2006).” As such, Behe argues, that evolutionary …natural selection can’t explain the origin of life from a simple entity to a complex organism. Since then, Christian apologists used Behe’s concept to argue for intelligent design. But my point is not to argue for it or against it. My aim is simply to use Behe’s a posteriori argument to illustrate for the gospel.…
-
ነገረ-ክርስቶስ በማርቆስ ወንጌል
[su_quote]ይህ ዐናጢው አይደለምን? የማርያም ልጅ፣ የያዕቆብና የዮሴፍ፤ የይሁዳና የስምዖን ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ እዚሁ እኛው ዘንድ አይደሉምን?” ከዚህም የተነሣ ተሰናከሉበት (ማር. 6:3)[/su_quote] ከዚህም የተነሣ ተሰናከሉበት፡ የማይለያዩት ‘ማንነቱና ሥራው’ በማርቆስ ወንጌል በመንግሥቱ ወንጌል መሰበክ አማካኝነት፤ በንሥሃ መንፈስ የተለወጠ ልብ ለሌለው ሰው የክርስቶስ ማንነት “ስውር” እንደሆን በማርቆስ ወንጌል ላይ እናያለን። ከሌሎቹ ወንጌላውያን ለየት ያለው ይህንን የማርቆስ አጽንኦት፣ የአዲስ ኪዳን ሊቃውንት “የእግዚአብሔር-ልጅ-ነገረ-ክርስቶስ”; “Son-of-God Christology (Lewis S. Hay)” ይሉታል። የወንጌሉ ምንባባዊ አወቃቀር የማርቆስን ወንጌል በሦስት አበይት ክፍሎች መመልከት እንችላለን፡ (1) የእግዚአብሔር ልጅ እና መሲሃዊ መንግሥቱ (1:1-15) – መግቢያ በዮርዳኖስ ወንዝ (2) የእግዚአብሔር ልጅ እና በእርሱ መሲሃዊ ዘመን በሃይል መፈንጠቁ (1:16-8:26) – በገሊላ (3) የእግዚአብሔር ልጅ እና መሲሃዊ መከራው (8:27-16:8) – በኢየሩሳሌም የመጀመሪያው ክፍል ላይ “የእ/ር…
-
በሁለት እውነታዎች ተወጥሮ የተቃኘ መንፈሳዊ ሕይወት (መስቀልና ዙፋን – ክፍል 3)
ከዚህ ቀደም “ዘራፍ ዘራፍ” የምትለውን ቤተክርስቲያን እና “በሽሽት ላይ ያለቸውን” ቤተክርስቲያን <<መስቀልን እና ዙፋን>> ያላማጠኑ ጽንፈኞች እንደሆኑ አይተን ነበር። ከወንጌላዊው ዮሐንስ ነገረ-መለኮታዊ ትረካም ወስደን፤ ወልድ ተልዕኮውን የሚፈጽምበት ሰዓት አይተናል። ይህም የመስቀሉ ሥራ ነው። ይህ ተልዕኮ ታላቅን መዳንን ገልጧል። ይህ አንድ ተልዕኮ እውነተኛውን አምላክ አብን እና ልጁን ወልድን የሚያሳይ ሥራ በመሆኑ፤ የድነት ሥራው አሰተርዕዮ ነው፤ ይህንን ማወቅ የዘላለም ሕይወት ነው። ይህንን ተመልክተናል። ሆኖም ግን ደግሞ ሦስቱ ወንጌላውያን (ማቴዎስ፤ ማርቆስና ሉቃስ) በእግዚአብሔር መንግሥት ዙሪያ በተቃኘ ዕይታቸው ይህንን ታላቅ መዳን ከሌላ ገጽታ አንጻር ይተርኩልናል። ኢየሱስ የነብያት ድምጽ እና የዳዊት ኪዳን ሊፈጽም መንግሥትን ይዞ በመገለጡ ላይ በማነጣጠር ፤ መዳን የእግዚአብሔር መንግሥት አሰራር እንደሆን ያሳዩናል (ማር 1:15)። ልክ በዮሐንስ ወንጌል “መስቀልና የዘላለም ሕይወት” የማይለያዩ ገጽታዎች…
-
አስተርዕዮተ-እግዚአብሔር እና ነገረ-ድነት
(ከማኅደር፡ አስቀድሞ በጥቅምት 2014 ተጻፈ) የዘላለም ሕይወት እግዚአብሔርን ማወቅ ነው _የዚህ ጽሑፍ መሠረታዊ ሐሳብ፡- መዳን እግዚአብሔርን ማወቅ ነው፤ ይህም በወንጌል አማካኝነት የተሰጠን ጥሪ ነው። _የዚህ ጽሑፍ ምጋቤያዊ ምልከታ፦ ድነት ሁሉን የሚዳሥ ሰፊ ፕሮጀችት ነው። ስለዚህ መዳን ሁለንተናችንን ይመለከታል። ለመዳን የሚያስችል እምነት አንድ፤ ለጉዳዮቻችንና ለሕይወታችን ደግሞ ሌላ ዓይነት እምነት የሚባል ነገር አይደለም። ለመዳን በክርስቶስ እንዳመንን፤ በዚያው እምነት በሕይወት እንኖራለን። ስለ እምነት እንደዚህ አይነቱ አመለካከት፤ አማክሎተ-ክርስቶስን ከአይናችን ዘወር ያደርጋል። በክርስቶስ ላይ ያለን እምነት የሁለንተናችን ማዕከል ነው፤ ከዚህ አናድግም፤ አንሻሻልም፤ ሥር እየሰደድን እናድጋለን እንጂ። ስለዚህ የእምነት ዓይነት የለም።እምነት 7 ደረጃዎች የሉትም! እምነት ክርስቶስን ማዕከል እንዳደረገ ውሎ፤ አድሮ ይሰነብታል፤ እስከ ሽበት! አንድ እምነት! ለዚያ ነው “ከእምነት ወደ እምነት” የተባልነው፤ አንዳንዶች እንዳሉት “ከአንድ ዓይነት እምነት…
-
ባሮክ ምን ጠይቆ ይሁን (ኤር. 45:5)?
וְאַתָּ֛ה תְּבַקֶּשׁ־לְךָ֥ גְדֹל֖וֹת אַל־תְּבַקֵּ֑שׁ כִּ֡י הִנְנִי֩ מֵבִ֨יא רָעָ֤ה עַל־כָּל־בָּשָׂר֙ נְאֻם־יְהוָ֔ה וְנָתַתִּ֨י לְךָ֤ אֶֽת־נַפְשְׁךָ֙ לְשָׁלָ֔ל עַ֥ל כָּל־הַמְּקֹמ֖וֹת אֲשֶׁ֥ר תֵּֽלֶךְ־שָֽׁם׃ ► ❝አንተ! ለገዛ ራስህ ታላላቅ ነገሮችን ትፈላልጋለህ? (ወይም ታላላቅ ነገሮች የምትመኝበት ጊዜ ነውን?) እነሆ እኔ ክፉ ጥፋት በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ እያመጣሁ ነውና እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን አትፈላልግ!” ይላል ኧዶናይ (ያህዌህ)። ይልቁንስ በእነዚያ በምትሔድባቸው ሥፍራዎች ሁሉ ላይ የገዛ ሕይወትህን እንደ ምርኮ አድርጌ ለራስህ እሰጣለሁ።❞ [የራሴ ትርጉም] ► Paraphrase: ❝ጊዜው አስጨናቂ የፍርድ ሰዓት በሰው ሁሉ ላይ እያመጣሁ መሆኑን እወቅ። ሕይወትህን አተርፋታለሁ፤ ስለዚህ የምትፈልገው ትልቅ ነገር ይህ ይሁንልህ እንጂ ሌላ ትልልቅ ነገሮችን ለራስህ አትፈላልግ! ይላል እግዚአብሔር❞ [የራሴ ትርጉም] የM.Div. ተማሪ ሳለሁ ስምንት የቋንቋና የፍታቴ በግሪክና በእብራይስጥ መውሰድ የግድ ነበረብኝ። ከእነዚያ ክፍሎች አቅብጦኝ የተመዘገብኩት የኤርሚያስን መጽሐፍ…