ፍታቴ/ Exegesis
Exegesis is the faithful reading of a specific text at hand, it simply means to lead-out the intended meaning. It is the opposit of Eisegesis, which means to infuse or to read-in meanings that are NOT there in the text, as such it is not the faithful reading of scripture. When we read the scripture we bring several presuppositions that are either good or bad. We don't come to the scripture clean. Therefore the principle of Exegesis (principle of interpretaion), help us rather first to recognize that we come with many baggages, some are influenced by those who taught us in the past, some are twisted by our sinful tendency that would want to have us read it in a certain way, and some are influenced by our own worldview, culture, language and upbringings. Therefore the principle of exegesis helps us filter out all those bad influences and prevent us from reading what we want the text to say. Rather this process brings us under the power and the absolute authority of the word of God, to hear it clear and to hear it well. I encourage you to pay attention to these principles well. "Our goal is not to be Masters of the Word, but to be Mastered by the Word" D. A. Carson
-
የዐደራ ኑዛዜ ክፍል አንድ፡ በወንጌል ዙሪያ የተደራጀ ሕይወትና ማንነት
2 ጢሞቴዎስ ሕይወትን የሚቃኝና ሕይወታችንን በቅደም ተከተል የሚያደራጅ መልዕክት ነው። መጽሐፉ ነገሮችን በጥቁርና በነጭ ቁልጭ አድርጎ የሚያስቀምጥ መልዕክት ነው። ለግራጫ ሥፍራ የለውም። “የሚቃኝ” ስንል ወደ ዋነኛ ጥሪያችን እንድንመለስ፣ ትኩረታችንን እንድናስተካክል፣ ዋነኛውን ዋነኛ እንድናደርግ፣ የከበረውን ከተዋረደው እንድንለይ የሚያደርገን መልዕክት ነው ማለታችን ነው። ዴማስ ወደ ተሰሎንቄ ምን ሊሰራ እንደሄደ አልተነገረንም። በአንድ ወቅት ግን እንደ ጢሞቴዎስ አብሮ የወንጌል ሰራተኛ ነበር (ቆላ 4፡14; ፊል…
-
«በእኔ ኑሩ፣ በፍቅሬ ኑሩ!» (ዮሐ. 15:9-17)
በቨርጂንያ በምትገኘዋ ‘የቃል ኪዳን ወንጌል ቤተ ክርስቲያን’ በዘመን መለወጫ ዋዜማ (12/31/2020) የተካፈልኩት ቃል ነው። በዚህ በያዝነው ዓመት የቤተ ክርስቲያን ልሳን የፍቅር እንዲሆን፣ የእርሱን ፍቅር ተረድተን ከግንዱ ጋር የምንጣበቅበት፣ ብዙ የምናፈራበት ይሁንልን። ከግንዱ ጋር የተጣበቀ እንጂ «ከውጪ ተለጣፊ ቅርንጫፍ» ፍሬ አያፈራም። ይህንን አብ ይቆርጠዋል። ግን በእርሱ የሚኖሩትን ፍሬ እንዲያፈሩ አብ ይገርዛቸዋል። ውድ ወዳጆቼ፣ ከእርሱ ጋር እንጣበቅ፣ በእርሱ እንኑር። እናፈራለንና። አሊያ “ያለ…
-
ባሪያዬ ይከብራል ከፍ ከፍም ይላል
“እነሆ፥ ባሪያዬ በማስተዋል ያደርጋል፤ ይከብራል ከፍ ከፍም ይላል፥ እጅግ ታላቅም ይሆናል።” (ኢሳያስ 52:13) አብዛኛውን ጊዜ ስለ ጌታ ባሪያ ሥቃይና መከራ ስናስብ የምንጠቅሰው ኢሳ 53:1-12 ነው። ሆኖም ግን ኢሳ 53 መጀመር የነበረበት በ53:1 ላይ ሳይሆን 52:13 ላይ ነበር። ይህን ማስተዋል ምን ፋይዳ አለው? ፋይዳው፣ በብሉይ ኪዳን ላይ ስለ ክርስቶስ ትንሳኤና ዕርገት በግልጽ ፍርጥ አድርገው ከሚናገሩ ጥቂት ክፍሎች መካከል (ከመዝ 110:1 ቀጥሎ)…
-
ቁጣው ተወግዶልሻልና ተነሺ! – ክፍል አንድ
ይህ ልጠፋዬ፣ በክፍል ሁለት ላይ ለምለጥፈው፣ በኢሳ 51:17-23 ላይ ላተኮረው ሐቲት፣ መግቢያና መንደርደሪያ እንዲሆን ነው። የምንባቡን ይዘት በጥልቀት ለመረዳት እንዲያስችል፣ ይህ ጽሑፍ የሚያተኩረው ‹አጠቃላይ ምንባባዊና ጽሑፋዊ አውድ› በመስጠት ላይ ነው። ከእግዚአብሔር እጅ፣ የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ፣ ዝቃጩ እንኳ ሳይቀር፣ ሰዎችን የሚያንገደግደውን ዋንጫ የጨለጥሽ፣ ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤ ተነሺ! ከወለደቻቸው ልጆች ሁሉ የሚመራት የለም፥ ካሳደገቻቸውም ልጆች ሁሉ እጅዋን የሚይዝ የለም። እነዚህ ሁለት…
-
የተሰቀለ-ክርስቶስ፡ ክርስቶስ እንደተሰቀለ ሆኖ በመልዕክታችን ይኑር
የአንደኛ ቆሮንቶስ 1:10 – 2:5 ሐቲት ኢየሱስን እንደ “ክርስቶስ” መቀበል እና እንደ “ተሰቀለ-ክርስቶስ” መቀበል ይለያያሉ። እኛ የምንሰብከው “የክርስቶስ መስቀል” ከሌሎች መስቀሎች እንዲለይ ያደረገው፤ “መሰቀል” የሚባለው እውነታ አይደለም (በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አይሁድ ወጣቶች ተሰቅለው ነበር – በተለይ በ4 ዓ.ዓ. አካባቢ ላይ)፤ ክርስቶስም የሚለው ቃል አይደለም (ብዙ መሲህ-ነኝ ባዮች ከኢየሱስ በፊት እንደ ስምዖን ወልደ-ጊዮራ ያሉ፣ በኋላም እንደ ስምዖን ወልደ-ኮኸባ ተነስተው ነበር) ይልቁንም…
-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-2)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) ባለፈው ክፍል፣ እግዚአብሔርን መግለጥ የሚችለው «ራሱ እግዚአብሔር ብቻ» እንደሆን ተመልክተናል። ስለዚህም ያለ አስተርዮ እግዚአብሔርን ማወቅ አንችልም። ስለ ነገረ-አስተርዕዮም (እግዚአብሔር ራሱን እንዴት እንደገለጠ) በቂ ግንዛቤ ካልያዝን ስለ እግዚአብሔር ያለን ግንዛቤ ሊዛባ ይችላል። ሁለቱ የተያያዙ ናቸው። ለምሳሌ በማርቲን ሉተር አስተሳሰብ ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበረው ነገር፦…
-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-1)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) “እግዚአብሔር ማን ነው?” ለሚለው ጥያቄ በቂ ያልሆነ ወይም የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖረን ከሚያደርጉን ነገሮች አንዱና ተቀዳሚው፤ ስለ ነገረ-አስተርዮ በቂ ያልሆነ ግንዛቤ መጨበጥ ነው። ለምን!? ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ማወቅ የምንችለው «እግዚአብሔር ራሱን የገለጠልን እንደሆነ» ብቻ ስለሆነ ነው። እግዚአብሔርንም መግለጥ የሚችለው ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህም ያለ…
-
ነገረ-ክርስቶስ በዕብራውያን መልዕክት: መቅድም
(The Christology of Hebrews: An Introduction) የእብራውያን መጽሐፍ የሹመት መጽሐፍ ነው። የመጽሐፉን ሙሉ ነገረ–መለኮታዊ ክብደት የሚሸከመው «በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ» የሚለው እውነታ ነው (ዕብ 1:3; 1:13; 8:1; 10:12-13; 12:2)። ኢየሱስ ከሁሉ እንደሚልቅ ሰባኪያችን ሲሞግት (ጸሐፊውን የምጠራው ሰባኪው በማለት ነው) የሚያቀርባቸው መሠረታዊ ማስረጃዎች በሙሉ በዚህ ልዕልና እና እውነታ ላይ የተመረኮዙ እንዲሁም የተቃኙ ናቸው። እውነታው «ተቀመጠ» (ኧካቲሰን | ἐκάθισεν)” (1:3) የሚለው ሲሆን፤…
-
ስለ አፈታት ጥቂት፡ ከምንባቡ ይዘት ጋር በቅርበት መተዋወቅ
ለአንዳንዶች ይጠቅም ስለሚችል፤ በአንድ ምንባብ ላይ ያተኮረ ትምህርት/ስብከት ሳዘጋጅ ወይም ጽሑፋዊ ሐቲት ስጽፍ፣ ጽሑፋዊ ዓውዱን ለማግኘት የምከተለው ቅደም ተከተል ከሞላጎደል በጥቂቱ እነሆኝ። መጠነኛ የቋንቋ ስልጠና ለወሰዱ ደግሞ አንዳንድ ይጠቅማሉ ብዬ ያሰብኳቸውን መርጃ መጻሕፍቶችንም እጠቁማለሁ ።ከዚህ ቀጥሎ የማሰፍረው በተከታታይ አለፍ አለፍ እያልኩ ስለ ምንባብ አተታተት የማቀርበው ይሆናል። የሚከተለው የመጀመሪያው መርህ ነው። #አንደኛ፡ ከምንባቡ ይዘት ጋር በቅርበት መተዋወቅ ወፍ በረር ትውውቅ (Big…
-
የይሁዳ መልክት – መንደርደሪያ ነጥቦች
መግቢያ “ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ። ከብዙ ጊዜ በፊት ለዚህ ፍርድ የተጻፉ አንዳንዶች ሰዎች ሾልከው ገብተዋልና፤ ኃጢአተኞች ሆነው የአምላካችንን ጸጋ በሴሰኝነት ይለውጣሉ ንጉሣችንንና ጌታችንንም ብቻውን ያለውን ኢየሱስ ክርስቶስን ይክዳሉ” የይሁዳ መጽሐፍ ይዘት በሦስት ወይም በአራት አበይት ክፍሎች ራሱን ይከፍላል ሠላምታና መግቢያ (1-3) –…
-
የሕዝቅኤል ትንቢትና ቅዱሳት መጻሕፍት
በእያንዳንዱ ትውልድ መቼም መጪና ሂያጅ፤ እንዲሁም ወቅታዊና ጊዜያዊ፤ የሆኑ አያሌ ጉዳዮች አሉ። በአንድ ወቅት መሠረት አድርገን የያዝነው በሌላ ደግሞ "አይ እርሱማ አሁን አይሰራም" እንባላለን። በዚህ በሕዝቅኤል መጽሐፍ ጥናት ክፍላችን ላይ ያተኮርነው - "ስለ ሕዝቅኤል መጽሐፍ፤ ከቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ጋር፤ ልናውቅ በሚገባን እና ዘመን መጠቅ በሆኑ በአራት የቅዱሳት መጻህፍት ባህርያት ላይ ነው" እነዚህ በተለይ በዘመናችን ቤተክርስቲያን ትኩረት ልትሰጣቸው የሚገቡ መሠረቶች ናቸው።…
-
የሕዝቅኤል መጽሐፍ ጥናት: የእግዚአብሔርን ክብር ማወቅ
ዕለቱ July 31, 593 ቅ.ዓ. ነው። ምናልባትም ሕዝቅኤል በእግዚአብሔር ፊት ልቡን ለማፍሰስ ወደ ኮቦር ወንዝ ዳር ሔዶ ሊሆን ይችላል። ይህም ይሆን ይህ የምናውቀው ነገር ቢኖር ሕዝቅኤል ካህን ወይም የካህን ልጅ እንደነበር እና ይህ ቀን ደግሞ የካህኑ 30ኛ የልደት ዓመቱ እንደሆን ነው። የካህኑ የቡዝ ልጅ እንደመሆኑ እድሜ ልኩን ለካህንነት ሲገዘጋጅ እንደ ኖረ መገመት አዳጋች አይደለም። ሆኖም ግን ከዓምስት ዓመታት በፊት በ597…
-
Confessing Jesus as the Son of God: In Christian and Muslim Context
This is my summary and brief response to a workshop I attended in 2013, taught by Dr. Donald A. Carson on the subject of the Sonship of Christ in Christian and Muslim context. Dr. Carson mentions three objectives. (1) It is important to try to find how one moves from exegesis to doctrinal confessions. Some systematic theologies assume the bible…
-
Yahweh quenches our thirst
The first invitations, here in Isaiah 55:1 “everyone who thirsts come to the waters” focus on the spiritual condition of those who would come, namely those who are “thirsty”. That means those who think they are satisfied and have everything they need, by definition are those who reject this invitation. Those who are truly thirsty are those who know that…
-
009-010: በፊቱ ቅዱሳንና ነውር አልባ እንሆን ዘንድ – ኤፌ. 1:4 (የኤፌሶን ምዕራፍ አንድ ጥናት)
ክፍል ሁለት፦ [የምንባርከው] የመጀመሪያ ምክኒያት ስለመረጠንና ልጆቹ እንሆን ዘንድ አስቀድሞ ስለወሰነን ነው (ኤፌሶን 1:4-6) 1.1 ቅዱሳን እንድሆን ዘንድ መርጦናልና (1፡4) [sz-ytvideo url=”https://www.youtube.com/watch?v=ONkZUWC39lg” theme=”dark” cover=”local” responsive=”y” autoplay=”n” loop=”n” fullscreen=”y” disablekeyboard=”n” disableiframe=”n” disablerelated=”n” delayed=”n” schemaorg=”n” /] እግዚአብሔርን የምንባርክበት የመጀመሪያ ምክንያት፡- አለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ በእርሱ መርጦናልና[καθὼς ἐξελέξατο ἡμᾶς ἐν αὐτῷ πρὸ καταβολῆς κόσμου] ከቁጥ.4-14 ድረስ ለምን እ/ር እንደሚባረክ ምክኒያቱን ይሰጣል። ምርጫ ከብሉይ ጀምሮ…