መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ-መለኮት (BT)
Biblical theology is a reading of the scripture that focuses upon the organic development of the process of the self-revelation of God. This discipline takes note of the historic progressiveness of the revelation process and the embodiment of revelation as the word of God within history; and the organic nature of the historic process observable in revelation. (A paraphrase definition from Geerhardus Vos)
-
የአዲስ ኪዳን ዳሰሳ
ማቴዎስ የፍጻሜ መጽሐፍ ነው። ማቴዎስ ኢየሱስን የእሥራኤልን ጥሪ፣ ተሥፋና ተልዕኮ ተላበሶ እንደ ተወለደ ያቀርብልናል። ስለዚህ ኢየሱስ እውነተኛ እሥራኤል ነው። የእሥራኤልን መሢሃዊ ዘር ወርሷል፣ የተለያዩ የብሉይ ኪዳን ተስፋዎችንና ጥብብቆሽን ወደ ፍጻሜ አድርሷል። ይኽም፣ ማቴዎስ “እንዲህ ተብሎ የተጻፈው ተፈጸመ” የሚለውን ቀመር 11 ጊዜ በመደጋገም የወንጌሉን ትኩረት ያሳየናል። የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ሆኖ ነው (2:2)፣ የተሰቀለውም የአይሁድ ንጉሥ ተብሎ ነው (27፡54)። ሲወለድ፣ ሲጠመቅና በክብር…
-
ኢየሱስና የቅዱሳት መጻሕፍት ትራኬ
This is part of a half day long teaching series conducted with my students, based on the redemptive historical narrative of the old testament, paying attention to the development of the royal seed promises of God, culminating on King Jesus as the exalted Messiah-Lord, resulting on worldwide blessing and judgement. በሚከተሉት ትምህርቶች መሲሃዊ ተስፋ ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ-መለኮት አንጻር ቀርቧል።
-
ኦሪትና ሥነ-አፈታታዊ መርሆው
-
እግዚአብሔርና ኪዳናቱ
-
ባሪያዬ ይከብራል ከፍ ከፍም ይላል
“እነሆ፥ ባሪያዬ በማስተዋል ያደርጋል፤ ይከብራል ከፍ ከፍም ይላል፥ እጅግ ታላቅም ይሆናል።” (ኢሳያስ 52:13) አብዛኛውን ጊዜ ስለ ጌታ ባሪያ ሥቃይና መከራ ስናስብ የምንጠቅሰው ኢሳ 53:1-12 ነው። ሆኖም ግን ኢሳ 53 መጀመር የነበረበት በ53:1 ላይ ሳይሆን 52:13 ላይ ነበር። ይህን ማስተዋል ምን ፋይዳ አለው? ፋይዳው፣ በብሉይ ኪዳን ላይ ስለ ክርስቶስ ትንሳኤና ዕርገት በግልጽ ፍርጥ አድርገው ከሚናገሩ ጥቂት ክፍሎች መካከል (ከመዝ 110:1 ቀጥሎ)…
-
ቁጣው ተወግዶልሻልና ተነሺ! – ክፍል አንድ
ይህ ልጠፋዬ፣ በክፍል ሁለት ላይ ለምለጥፈው፣ በኢሳ 51:17-23 ላይ ላተኮረው ሐቲት፣ መግቢያና መንደርደሪያ እንዲሆን ነው። የምንባቡን ይዘት በጥልቀት ለመረዳት እንዲያስችል፣ ይህ ጽሑፍ የሚያተኩረው ‹አጠቃላይ ምንባባዊና ጽሑፋዊ አውድ› በመስጠት ላይ ነው። ከእግዚአብሔር እጅ፣ የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ፣ ዝቃጩ እንኳ ሳይቀር፣ ሰዎችን የሚያንገደግደውን ዋንጫ የጨለጥሽ፣ ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ተነሺ፤ ተነሺ፤ ተነሺ! ከወለደቻቸው ልጆች ሁሉ የሚመራት የለም፥ ካሳደገቻቸውም ልጆች ሁሉ እጅዋን የሚይዝ የለም። እነዚህ ሁለት…
-
ልደቱና የእግዚአብሔር ተስፋ ቃሎች (ኪዳንና ትሥጉት)
ሐዋሪያው ጳውሎስ “እግዚአብሔር ለሰጠው የተስፋ ቃል ሁሉ አዎን ማለት በእርሱ ነውና” ይለናል (2 ቆሮ. 1:20)። ያለ ኢየሱስ የተስፋ-ፍጻሜ የለም። ማንም ኢየሱስን ዘሎ በቀጥታ የእግዚአብሔርን ተስፋ የሚወርስ ፈጽሞ ሊኖር አይችልም። ያለ ኢየሱስ የሚጠብቀን “ፍርድና ርግማን” ብቻ ነው። በብሉይ የተሰጡትን ተስፋዎች ሁሉ አንድ አማኝ የሚቀበለው “በክርስቶስ” ውስጥ ነው። ይህንን ለማስረዳት፣ በምናባችን “ማጥለያ” እናስብ። ከላይ የሚጨመረው ዘይት ወደ ጠርሙሱ ጠሎ የሚገባው በማጥለያው ጠባብ…
-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-2)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) ባለፈው ክፍል፣ እግዚአብሔርን መግለጥ የሚችለው «ራሱ እግዚአብሔር ብቻ» እንደሆን ተመልክተናል። ስለዚህም ያለ አስተርዮ እግዚአብሔርን ማወቅ አንችልም። ስለ ነገረ-አስተርዕዮም (እግዚአብሔር ራሱን እንዴት እንደገለጠ) በቂ ግንዛቤ ካልያዝን ስለ እግዚአብሔር ያለን ግንዛቤ ሊዛባ ይችላል። ሁለቱ የተያያዙ ናቸው። ለምሳሌ በማርቲን ሉተር አስተሳሰብ ውስጥ ቁልፍ ሚና የነበረው ነገር፦…
-
በልጅ አንደበት ተናገረን፡ ወንጌልና አስተርዕዮ በእብራውያን መልዕክት (ክፍል-1)
«ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጎዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናግሮ…በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን» (ዕብ 1፡1:1-2) “እግዚአብሔር ማን ነው?” ለሚለው ጥያቄ በቂ ያልሆነ ወይም የተሳሳተ አመለካከት እንዲኖረን ከሚያደርጉን ነገሮች አንዱና ተቀዳሚው፤ ስለ ነገረ-አስተርዮ በቂ ያልሆነ ግንዛቤ መጨበጥ ነው። ለምን!? ምክኒያቱም እግዚአብሔርን ማወቅ የምንችለው «እግዚአብሔር ራሱን የገለጠልን እንደሆነ» ብቻ ስለሆነ ነው። እግዚአብሔርንም መግለጥ የሚችለው ራሱ እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህም ያለ…
-
ነገረ-ክርስቶስ በዕብራውያን መልዕክት: መቅድም
(The Christology of Hebrews: An Introduction) የእብራውያን መጽሐፍ የሹመት መጽሐፍ ነው። የመጽሐፉን ሙሉ ነገረ–መለኮታዊ ክብደት የሚሸከመው «በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ» የሚለው እውነታ ነው (ዕብ 1:3; 1:13; 8:1; 10:12-13; 12:2)። ኢየሱስ ከሁሉ እንደሚልቅ ሰባኪያችን ሲሞግት (ጸሐፊውን የምጠራው ሰባኪው በማለት ነው) የሚያቀርባቸው መሠረታዊ ማስረጃዎች በሙሉ በዚህ ልዕልና እና እውነታ ላይ የተመረኮዙ እንዲሁም የተቃኙ ናቸው። እውነታው «ተቀመጠ» (ኧካቲሰን | ἐκάθισεν)” (1:3) የሚለው ሲሆን፤…
-
የተሾመው መልከ ጼዴቃዊው ካህንና ንጉስ፡ የእብራውያን መጽሐፍ ዳሰሳ
-
መስቀልና ኪዳን፡ የመጨረሻው እራት
[su_quote]እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ [16] እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው (ሉቃስ 22:15-16)[/su_quote] ይህ እራት እጅግ የከበረ እራት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ሲናገር ❝ከእንጀራው ይብላ ከጽዋውም ይጠጣ፤ [ግን] ሳይገባው የሚበላና የሚጠጣ የጌታን ሥጋ ስለማይለይ ለራሱ ፍርድ ይበላልና፥ ይጠጣልምና❞ ይህ የሚያሳየን ይህ የመጨረሻው እራት ሥርዓት ብቻ ሳይሆን፣ በመረዳትና ተገቢ በሆነ መንገድ…
-
መስቀልና ኪዳን፡ የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች በአንድነት እንዲሰበስባቸው
“በዚያችም ዓመት ሊቀ ካህናት የነበረ ቀያፋ የሚሉት ከእነርሱ አንዱ። እናንተ ምንም አታውቁም፤ ሕዝቡም ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለ ሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡም አላቸው። ይህንም የተናገረ ከራሱ አይደለም፥ ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው ትንቢት ተናገረ፤ ስለ ሕዝቡም ሁሉ አይደለም፥ ነገር ግን የተበተኑትን የእግዚአብሔርን ልጆች ደግሞ በአንድነት እንዲሰበስባቸው ነው እንጂ። እንግዲህ ከዚያ ቀን ጀምረው…
-
የተሰቀለ-ክርስቶስ
ዛሬ እንደ ግሪጎሪያን አቆጣጠር የክርስቶስ የስቅለት ቀን ነው። በዚህ ቀን አንድ ጸሎት አለኝ “የዚህ ቀን እውነታ ሳያቋርጥ በዘመናችን እና በትውልዳችን እንዲቀጥል…ክርስቶስ እንደተሰቀለ ሆኖ በመልዕክታችን እንዲኖር! (ገላ 3:1 |፡1 ቆሮ. 2:2-3)” ኢየሱስን እንደ ክርስቶስ መቀበል እና እንደ ተሰቀለ-ክርስቶስ መቀበል ይለያያሉ። እኛ የምንሰብከው “የክርስቶስ መስቀል” ከሌሎች መስቀሎች ልዩ ያደረገው፤ “መሰቀል” የሚባለው እውነታ ሳይሆን (በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አይሁድ ወጣቶች ተሰቅለው ነበር – በተለይ…
-
የብሉይ ነቢያት ጥሪ፣ መልክዕክት እና መጻሕፍት
ይህ ትምህርት ከጥቂት ወራት በፊት “የነቢያት ጥሪ፤ መልዕክት እና መጻሕፍት” በሚል ርዕስ ስለ ብሉይ ትንቢት መጻሕፍት ወደ 4.5 ሰዓት የፈጀ ትምህርት ለዴንቨር የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት LIVE ያስተማርሁት ነበር። አስቀድሜ ይህንን ትምህርት እንዳስተምር የጋበዘኝን ፓስተር ኤርሚያስ አማኑኤልን ከልብ እያመሰገንሁ ሌሎችም ትምህርቱን ማዳመጥ እንዲችሉ በማሰብ እንደገና ተቀድቶ፤ አሁን ከጥናት ጹሑፍ ጋር በአንድ ላይ ተቀናብሯል። ❝እንግዲያስ ትንቢታዊው ቃል ይበልጥ…