
009-01: The Person of YHWH:- To know Him is to have Eternal Life
[ap_tab_group type=”horizontal”]
[ap_tab title=”Audio”] [/ap_tab]
[ap_tab title=”Excerpt”]Salvation is a relational knowledge of God. In salvation, we are being elevated from our sinful status to a status of glory. The status of our glory was accomplished by the Son leaving the glory he had with the father eternally, which was intrinsic to his own person. He did this in order to do his father’s bidding to a lowly/ impoverished status that was foreign to his own person (John 17:19, Phil 2:9-11) and having accomplished His mission through the ignominious death on the cross, he was glorified in order to glorify the father by glorifying us.
In summary salvation is a personal-knowledge of the Triune God, an intimate union with the Father and the Son through his personal word (message) that he left us through the apostles and the personal indwelling presence of the Holy Spirit abiding in us.[/ap_tab]
[ap_tab title=”Scriptural References”]
John 17:3
1 John 4:8–10
John 17:7–8, 26
[/ap_tab]
[/ap_tab_group]
፩
እግዚአብሔርን ማወቅ የነገር ሁሉ ግብ ነው
ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት!
“ኢየሱስም ይህን ተናግሮ ወደ ሰማይ ዓይኖቹን አነሣና እንዲህ አለ። አባት ሆይ፥ ሰዓቱ ደርሶአል፤ ልጅህ ያከብርህ ዘንድ፥ በሥጋም ሁሉ ላይ ሥልጣን እንደ ሰጠኸው፥ ለሰጠኸው ሁሉ የዘላለምን ሕይወት ይሰጣቸው ዘንድ ልጅህን አክብረው። እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ”
በዚህ በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ “ሰዓት” የሚለው ቃል ከሌሎቹ ወንጌላውያን ለየት ያለ ትኩረትና በዮሐንስ-ነገረ መለኮታዊ ትረካ ውስጥ እያደገ የመጣ ሐሳብ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ሰዓት ከወልድ ተልዕኮ ጋር የተያያዘ ጥልቅ መለኮታዊ እውነትን የሚያንጸባርቅ ቃል ነው። ለምሳሌ ያህል፤ ለማርቆስ የሰዓቱ መድረስ (ማር 1:15) ከነብያት ድምጽ ጋር በማገናኘት (ማር 1፡2-3)፤ በኢየሱስ ማንነትና አገልግሎት (አገልግሎት የሚለውን ቃል ለክርስቶስ ስጠቀም በቃልና በሥራ የተሰጠውን የክርስቶስን መለኮታዊ አስተርዕዮ ማመልከቴ ነው – what some call the ‘Christ-event’) የእሥራኤልን ተሥፋ በሰውነቱ ለብሶ መገለጡን ይገልጻል። ስለዚህ በማርቆስ ወንጌል ሰዓት በክርስቶስ (የዳዊት ልጅ -መዝ 2፡7/ 2ሳሙ 7:14) አገልግሎት (በማንነቱ፤ በቃሉናና በሥራው) አማካይነት የእግዚአብሔር መንግሥት መጥባቱን ያውጃል። እግዚአብሔር የሰጣቸው የማዳን ተስፋዎች ሁሉ አሁን በገሊላ አውራጃ እየተፈጸሙ መሆናቸውን ያውጃል። ይህም የወንጌል መጀመሪያ ነው።
ወንጌላዊው ዮሐንስ ግን የክርስቶስን ማንነት ከድንግል ከመወለዱ (ወይም ከትሥጉት) አንድ እርምጃ ዕምር ብሎ ከሥነ-ፍጥረት መጀመሪያ ይጀምራል። እንደዚሁም የክርስቶስን አገልግሎት ትረካ ከገሊላው አገልግሎት ፈቀቅ አድርጎ ከአንድ የሰርግ በዓል ድግስ ይጀምራል። በዚህ መጽሐፍ ክብር፤ ምልክት፤ የአብ ፈቃድ መፈጸም፤ የወልድ ተልዕኮ፤ መውጣትና መውረድ፤ የመስቀሉ ውርደት፤ የዘላለም ሕይወት ከዚህ አንድ ቃል -ሰዓት- ጋር የተያያዙ ናቸው። ሆኖም ግን ይህች ሰዓት በዮሐንስ የነገረ-መለኮት ትረካ ውስጥ ከሰው ልጅ አገልግሎት መጀመሪያ ጋር ሳይሆን ከሰው ልጅ ታልፎ ከሚሰጥባት ለሊት ጋር የተያያዘች ነች። ለምሳሌ ያህል የመጀመሪያውን ምልክት ሲያደርግና ደቀ መዛሙርቱ በእርሱ ሲያምኑበትና ክብሩን ሲያዩ ይህች ሰዓት ገና አልደረሰችም፡
- “የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፤ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው። ኢየሱስም፤ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት” ዮሐ 2:3-4
- (“οὔπω ἥκει ἡ ὥρα μου” የአዲሱ መደበኛ ትርጉም ‘ሰዓቴ’ ሆራ-ሙ’ ለሚለው የግሪኩ ቃል ይበልጥ ይቀርባል)
- ስለዚህ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አልጫነበትም። ከሕዝቡ ግን ብዙዎች አመኑበትና። ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ይህ ካደረጋቸው ምልክቶች ይልቅ ያደርጋልን? አሉ። (John 7:30–31)
- ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ፤ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም። ኢየሱስም ደግሞ። እኔ እሄዳለሁ ትፈልጉኛላችሁም በኃጢአታችሁም ትሞታላችሁ እኔ ወደምሄድበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አላቸው። (John 8:20–21)
ሆኖም ግን ይህች ሰዓት መድረሷን አብ ለሚወደው ልጁ “ኢየሱስን ልናይ እንወዳለን” ብለው በመጡት በግሪክ ሰዎች አመለከተው። ይህም አሕዛብ ወደ ኪዳኑ በረከት መጠጋታቸው ለአብርሃም የተሰጠውን የተሥፋ ቃል አሁን በወልድ የመስቀል ተልዕኮ የሚፈጽምበት ሰዓት መድረሱ ሲያመላክት
- ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል። የሰው ልጅ ይከብር ዘንድ ሰዓቱ ደርሶአል። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የስንዴ ቅንጣት በምድር ወድቃ ካልሞተች ብቻዋን ትቀራለች፤ ብትሞት ግን ብዙ ፍሬ ታፈራለች።… አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ? ነገር ግን ስለዚህ ወደዚህ ሰዓት መጣሁ። አባት ሆይ፥ ስምህን አክብረው። ስለዚህም። አከበርሁት ደግሞም አከብረዋለሁ የሚል ድምፅ ከሰማይ መጣ…አሁን የዚህ ዓለም ፍርድ ደርሶአል፤ አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጭ ይጣላል፤ እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ። በምን ዓይነትም ሞት ይሞት ዘንድ እንዳለው ሲያመለክታቸው ይህን ተናገረ። John 23:27–33
- ኢየሱስም ከፋሲካ በዓል በፊት፥ ከዚህ ዓለም ወደ አብ የሚሄድበት ሰዓት እንደ ደረሰ አውቆ፥ በዚህ ዓለም ያሉትን ወገኖቹን የወደዳቸውን እስከ መጨረሻ ወደዳቸው። (John 13:1)
ከዚህ ወደ ጥልቅ ጅረት ከሚወስደን ዋና እንውጣና ወደ ጀመርንበት እምር እንበል። ወልድ ወደ መስቀል ከመውጣቱ በፊት ሲጸልይ (የታላቅ-ሊቀ-ካህናት ጸሎት) መጀመሪያ ከአፉ የወጣው ቃል “አባት ሆይ ሰዓቱ ደርሶአል” ነበር። የዚህች ሰዓት ትልቅነት የተመሰረተው በዚህች ሰዓት ውስጥ የሚከናወነው ሥራ ነው።
- መለኮታዊ ተልዕኮ ነው፡- ይህ ሥራ አለም ሳይፈጠር አብ ለወልድ የሰጠውና በአገልግሎቱ አብ ሲያሳየው (ዮሐ 5:19-39) ለነበረው ሥራ ጫፍ ነው። በዚህ ተልዕኮ አብ ይከብራል። ይህም የመስቀሉ ተልዕኮ ነው። “የሰው ልጅ ከምድር ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ” የሚለው ሐረግ ዮሐንስ እንደዘወትሮው ድርብ ትእምርትን በመጠቀም የክርስቶስ ውርደት የክብር ጎዳና እንደሆነ ያሳየናል። የሮማውያን ወታደሮች መስቀሉን በገመድ ወደ ላይ ከፍ እያደረጉ ወልድን በአየር ላይ ሲያንጠለጥሉት፤ በዚህ አንድ የውርደት መስቀል ላይ ወልድ የአባቱን ሥራ በፈጸሙ የሚከብርበትም መንገድ ነው። ሥለዚህ መስቀሉ የክብር ጎዳና ነው። በዚህ መንገድ ወልድ ይዋረዳል፤ አብ ይከብራል፤ ወልድን አብ ዓለም ሳይፈጠር በነበረው ክብር መልሶ ያከብረዋል፤ በሰዎች ልጆች ሁሉ ላይ ሥልጣን ይጎናጸፋል፤ የዚህ ዓለም ገዚ ወደ ውጪ ይጣላል!
- መለኮታዊ አስተርዕዮ ነው፡- በዚህች ሰዓት በተገለጠው ሥራ ውስጥ እውነተኛው አምላክ አብና የተላከው ወልድ ተገልጠዋል።
- የዘላለም ሕይወት ነው፡’ ምልክቶቹ የተሰጡበት ዓላማ አንባቢው፡ ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ ውጤቱም በስሙ የዘላለምሕይወት ይሆንልን ዘንድ ነው
- ዘላለማዊ ሕይወት ኢየሱስ ዳግም ሲገለጥ ዕውን የሚሆነው የመጪው ዘመን ሕይወት ማለት (The Life of the age to come, “zoe-aionios”)
- ስለ እኔና ስለ ወንጌል ቤትን ወይም ወንድሞችን ወይም እኅቶችን ወይም አባትን ወይም እናትን ወይም ሚስትን ወይም ልጆችን ወይም እርሻን የተወ፥ 30 አሁን በዚህ ዘመን ከስደት ጋር ቤቶችን ወንድሞችንና እኅቶችንም እናቶችንም ልጆችንም እርሻንም መቶ እጥፍ፥ በሚመጣውም ዓለም/ዘመን የዘላለም ሕይወት የማይቀበል ማንም የለም። “31 ግን ብዙ ፊተኞች ኋለኞች ኋለኞችም ፊተኞች ይሆናሉ።” ማር 10፡ 30-31
- እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። “እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ”
ከዚህ የተነሳ የዘላለም ሕይወት ከላኪው አብና ከተላኪው ወልድ ጋር የተቆራኘ ነው። ያለ ወልድ ሕይወት የለም። ሆኖም ግን ልንገነዘበው የሚገባው ነገር፤ አብንና ወልድን ማወቅ ያለው ወልድ በሰጠን ቃሎቹና በፈጸማቸው ሥራዎች ውስጥ መሆኑን ነው። ዮሐንስ የአንድያ ልጁ የሆነውን ክብሩን ያየነው በምልክቶቹ (በሥራዎቹ) ውስጥ እንደሆን ያሳየናል። ሰዎች ክብሩን እንዴት አዩ? ወልድ ከባህር አጠገብ በጀልባ ቁጭ ብሎ፤ ታዳሚው አንድ በአንድ በአጠገቡ እያለፉና አፋቸውን በእጃቸው እየጫኑ፤ “አቤት የእግዚአብሔር ልጅ?” እያሉ ነበር? ታስታውሱ እንደሆን ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ሲሰብሰቡ ማቴዎስ ሲነግረን “አፉንም ከፍቶ አስተማራቸው እንዲህም አለ…” ትምሕርቱንም ሲጨርስ ሰዎች “ኢየሱስም ይህን ነገር በጨረሰ ጊዜ ሕዝቡ በትምህርቱ ተገረሙ፤ እንደ ጻፎቻቸው ሳይሆን እንደ ባለ ሥልጣን ያስተምራቸው ነበርና” ይላል። ስለዚህ ሕይወት ያለው ወልድን በማወቅ ውስጥ ነው። ወልድንም ማወቅ በቃሉና በሥራው ላይ ያነጣጠረ ነው። የእግዚአብሔር ሕዝብ አብ የሚወደውንና ወደ ዓለም የላከውን አንድያ ልጁን እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት የፈጸመውን ተልዕኮ ማወቅ እንዲሁ ግርድፍ ያለ እውቀትና ቃል ብቻ ሳይሆን ሕይወትን የሚሰጥና ለማዳን የሚችል መለኮታዊ ሐይል ነው።
- በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና። ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። (1 John 4:7–10)
የብሉይ ኪዳን ራዕየ-መለኮትና የአዲስ ኪዳን የሁለቱ አካላት ተልዕኮ
እዚህ ጋር ነካ አድርጌ ላልፍ የምፈልገው ነገር ቢኖር (እጅግ ሰፋ ያለና የረቀቀ እውነት ቢሆንም በአጭሩ) የወልድ ተልዕኮ ምንም እንኳ የመዋጀት ተልዕኮ ቢሆንም፤ ነገር ግን ይህ አንዱ የውጆት ተልዕኮ እግዚአብሔር ራሱን የገለጠበትም መንገድ እንደሆነ ጭምር ነው። ይህም የወልድ ተልዕኮ የሥሉሱ አምላክ አስተርዕዮ ነው። ለምሳሌ ያህል፤ እሥራኤአውያን ከግብጽ ባርነት ሲዋጁ ያህዌህ ኤሎሂም “ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ፥ አምላክም እሆናችኋለሁ፤ እኔም ከግብፃውያን ባርነት ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።” Exodus 6:7። ይህ ማለት በአንዱ የዘጸዓት ትድግና ሥራ ውስጥ (እዚህ ጋር የሙሴን ተልዕኮና የወልድን ተልዕኮ ማነጻጸር ተገቢ ነው) እሥራኤላውያን አምላካቸውን እንደ ያህዌህ ያውቁታል። ምክኒያቱም ከዚህ ቀደም ራሱን ሲገልጥ ያህዌህ ሁሉን እንደሚችል እንደ ኤልሻዳይ እንጂ (እዚህ ጋር ዘፀ 3:14-15 እና ዘፀ 6:2 አወዳድሩ) በቃል ኪዳን ሥሙ አልተገለጠም ነበርና ነው። ይህ ማለት ያህዌህ ሕዝብን ገንዘቡ አድርጎ፤ የሕዝብ አምላክ ሆኖ መገለጡ(የሕዝቡ የቃል ኪዳን ጌታ – in this Exodus narrative, you have here the beginning of sonship language applied to a nation present, unlike the Genesis narrative) የዘጸዓቱ ትድግና የቃል ኪዳን ሥሙን ፍንትው አድርጎ መግለጡን ያስያል። ከዚህ የተነሳ ያህዌህ ለአባቶች (ለአብርሃም፤ ይሥሐቅና ያዕቆብ) ሲገለጥ (ሲናገርና ሲሰራ) በመገለጡ ውስጥ ስለሚያመልኩት አምላክ የሚተላለፍም እውነት አለ። ያህዌህ ለአባቶች ተገለጠ (ዘፍ 17፡1-2፤ 35፡9-13) በሚሉት ሥፍራዎች ላይ እንደ ኤልሻዳይ እንደተገለጠ ጸሐፊው ይነግረናል (ወደ ፊት ሰፋ አድርጌ እገልጸዋለሁ)። የዘጸዓቱ ትድግና ግን ለቅዱሱ ስም ያህዌህ መገለጥ የሚመጥን ሥራ መሆኑን እናያለን። ስለዚህ የእስራኤል መዋጀት ግቡ እስራኤል እግዚአብሔርን ማወቋ ነበር። ትድግናው አስተርእዮ አዝሏል ማለት ነው። (በዘጸዓት መጸሐፍ ስሙን የሕዝብ-አምላክ ከመሆኑ፤ ከአብሮነቱና ከ ‘ያውነቱ’ ያገናኘዋል)። አሁንም ጌታችን ሊፈጽመው ባለው ዳግም-ጸዓት (ሁለተኛ ትድግና) ተልዕኮ ውስጥ የስሉሱ አምላክ መገለጥ ያዘለ ትድግና ነው።
የዘላለም ሕይወት እግዚአብሔርን ማወቅ ነው
የዚህ ቀደሙ ኪዳን ድክመት የተመሰረተው በኪዳኑ መካከል ከቆሙት መልዕክተኞች የተነሳ ነው። በኪዳኑ መካከል የእግዚአብሔር መልአክ እና የቃል ኪዳን መልዕክተኞች ሁሉ ቁንጮ የሆነው ሙሴ ነበሩና ነው። በዚህ ኪዳን መልዕክቱም እንዲሁ አስተርዕዮውም መለኮታዊ ነበሩ። ሆኖም ግን የመገለጡ ተረካቢዎቹና ገላጮቹ ግን መለኮታዊ አይደሉም። ከዚህ የተነሳ በልጁ የተመረቀውን ኪዳን የላቀ ኪዳን እንደሆን የዕብራውያን ጸሐፊ ሲናገር “ስለዚህ ከሰማነው ነገር ምናልባት እንዳንወሰድ፥ ለእርሱ አብልጠን ልንጠነቀቅ ያስፈልገናል። በመላእክት የተነገረው ቃል ጽኑ ከሆነ፥ መተላለፍና አለመታዘዝም ሁሉ የጽድቅን ብድራት ከተቀበለ፥ እኛስ እንዲህ ያለውን ታላቅ መዳን ቸል ብንለው፥ እንዴት እናመልጣለን?” (Hebrews 2:1–2፟) ይለናል። የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ክርስቶስ ነው። መጥምቁ ዮሐንስ ጣቱን ጦቁሞ “እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል። ከላይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው፤ ከምድር የሚሆነው የምድር ነው የምድሩንም ይናገራል። ከሰማይ የሚመጣው ከሁሉ በላይ ነው። ያየውንና የሰማውንም ይህን ይመሰክራል፥ ምስክሩንም የሚቀበለው የለም (John 3:30–32)” ቃሎቹ የእግዚአብሔር ቃሎች ናቸው። ሥራዎቹ የእግዚአብሔር ሥራዎች ናቸው። እግዚአብሔር ከሰማይ የላከው ይህ የእግዚአብሔርን ቃል ይናገራልና፤ መንፈሱንም ሲሰጠው አይሰፍርምና! የፊደሉ ሕግ አሁን በመንፈስ ሕግ ተተክቷል። (ይህ ማለት ጨርሶ ትእዛዛት ሥፍራ የላቸውም ማለት ወይም የሕጉን መጽሐፍ አናነብም ማለት አይደለም። ሆኖም ግን ሕግ እንደ ኪዳን (law covenant) ሊፈጽም ያልቻለውን ልጁንና መንፈሱን ልኮ የሕግን አላማ በእኛ በመንፈስ ለምንመራና በክርስቶስ ለምናምን እውን ይሆናል) እግዚአብሔር ያድነን ዘንድ መልአክ አልላከም። ከላይ እንደተመለከትነው በዚህም አንድ ተልዕኮ ውስጥ አብ ሁለት መልዕክተኞችን ልኳል። “በዘመኑ ፍጻሜ ግን ከሴት የተወለደውን ከሕግ በታች የሆነውን ልጁን ላከ….አባ አባት ብሎ የሚጮሀውን የልጁን መንፈስ ወደ ልባችን ላከ! ገላ 4:4” እነዚህ ሁለት አካላት እንደ እግዚአብሔር መልአክ ወይም እንደ ሙሴ ከውጪ ሰምተው እግዚአብሔርን የሚገልጡ ሳይሆኑ፤ መግለጣቸውም መገለጡም ሙሉ በሙሉ መለኮታዊ ነው። ምክኒያቱም ሁለቱም አካላት ከአብ ጋር አንዱ ሕላዌ ገንዘባቸው ስለሆነ ነው። ከዚህ የተነሳ የወልድ ቃል ከብሉይ ሕግና ከነብያት ቃል እጅጉን ይልቃል “ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር፤ እርሱ ስለ እኔ ጽፎአልና። መጻሕፍትን ካላመናችሁ ግን ቃሌን እንዴት ታምናላችሁ?” (John 5:46–47)። ከ11ኛው ክፍለዘመን ቤተክርስቲያን አበው መካከል እንደ ምሶሶ ተደርገው ከሚቆጠሩት መካከል አንዱ የሆነው“ከካንትቤሪ የሆነው አንሰልም” “ለምን አምላክ ሰው ሆነ?- ‘Cur Deus Homo” በተሰኘው መጽሀፉ ከብዕር ጓደኛው ጋር ሲወያይ እንዲህ ብሎ ጻፈ፡ (ለመተርጎም ልሞክር)
“የሰው ልጆች መዋጀት ከራሱ ከእግዚአብሔር በስተቀር በሌላ ሰው አሊያም መልአክ አማካይነት ሊከናወን አይችልም። ከእግዚአብሔር ሌላ የሆነ አካል ሆኖ ቢሆን ከዘላለም ሞት ያዳነን፤ የዳኑት ለዚህ ላዳናቸው አካል (ሰው ወይም መልአክ) አዳኜ ብለው ባርያ በሆኑለት ነበር። ታድያማ ይህ እንዴት መዳን ይባላል! ምክኒያቱም የዳኑት ከእግዚአብሔር ሌላ ለሆነው ባርያ ናቸውና። ይህ አሁን እንደሆነው ማለት ነው…በአየሩ ላይ ላለው አለቃ ሰዎች ይገዛሉና ”
ይህ የቤተ-ክርስቲያን አባት አስምሮ የተናገርው ነገር ምንድር ነው፤ የሰው ልጆች ሐጥያት እምብርት አመጽ ስለሆነ፤ ይህም ለእግዚአብሔር አለመገዛት፤ ከእግዚአብሔር ሥልጣንና አገዛዝ ማፈንገጥ፤ የእግዚአብሔርን ክብር በሌላ በተፈጠሩ ነገሮች እንደዚሁም የእግዚአብሔርን መለኮታዊ እውነት በሐሰት መለወጥ እስከሆነ ድረስ፤ እውነተኛ መዋጀት እነዚህ ነገሮች ያስተካከለ እንደሆን ብቻ ነው። ሰው ወደ እግዚአብሔር ሥልጣን ሲመለስ፤ ተንበርክኮ ይህንን አምላክ አዳኜ ያለ እንደሆን ብቻ ነው። አንሰልም ጥሩ አይቷል። በነብዩ ኢሳያስም ያህዌህ እንዲህ ይላል
- እናንተ ከአሕዛብ ወገን ሆናችሁ ያመለጣችሁ፥ ተሰብስባችሁ ኑ በአንድነትም ቅረቡ፤ የተቀረጸውን የምስላቸውን እንጨት የሚሸከሙና ያድን ዘንድ ወደማይችል አምላክ የሚጸልዩ እውቀት የላቸውም። ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ፤ ከጥንቱ ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማን ነው? ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ እኔ ጻድቅ አምላክና መድኃኒት ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም። እናንተ የምድር ዳርቻ ሁሉ፥ እኔ አምላክ ነኝና፥ ከእኔም በቀር ሌላ የለምና ወደ እኔ ዘወር በሉ ትድኑማላችሁ። ቃሌ ከአፌ በጽድቅ ወጥታለች፥ አትመለስም። ጕልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል፥ ምላስም ሁሉ በእኔ ይምላል ብዬ በራሴ ምያለሁ። ስለ እኔም። በእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ጽድቅና ኃይል አለ፥ ወደ እርሱም ሰዎች ይመጣሉ፥ በእርሱም ላይ የተቈጡ ሁሉ ያፍራሉ። የእስራኤልም ዘር ሁሉ በእግዚአብሔር ይጸድቃሉ፥ ይመካሉም ይባላል” (Isaiah 45:20–25)
ስለዚህ እውነተኛ መዳን ሁለት ነገሮችን ያቅፋል። እነዚህ ሁለት እውነታዎችን በብዙ መንገድ አዲስ ኪዳን ያሰቀምጣቸዋል። ለግልጽነት እንዲመች ግን ሁለት መደቦችን ልጠቀም። በአንድ እጅ እነዚህን ቃሎች እንያዝ፦ መጽደቅ፤ መዋጀት፤ እርቅ፤ ሰላም፤ መግባት፤ ሥርየት። በሌላ እጅ ደግሞ መክበር፤ ልጅነት፤ ተስፋ፤ ርስት። እነዚህ ሁለት እውነታዎች የሚያንጸባርቁት በአንድ ወገን ከየት እንደመጣን ሲሆን በሌላ እጅ ደግሞ ወዴት እንደምንሔድ ነው። በአንድ ወገን ድነናል በሌላ ወገን ደግሞ ገና በሙላት እንድናለን። መጽሀፍ ቅዱሳዊ ደህንነት ‘ከ’ እና ‘ወደ’ የሚሉትን መስተዋድዶች ገንዘቡ ማድረግ አለበት።
- እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል። ስለዚህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ መጠራታችሁንና መመረጣችሁን ታጸኑ ዘንድ ከፊት ይልቅ ትጉ፤ እነዚህን ብታደርጉ ከቶ አትሰናከሉምና። እንዲሁ ወደ ዘላለሙ ወደ ጌታችንና መድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ መንግሥት መግባት በሙላት ይሰጣችኋልና (2 Peter 1:9–11)
ክርስቶስ ራሱን መስዋዕት አድርጎ በማቅረብ ለሐጥያታችን ሥርየት ሲል “ሐጥያታችንን በእንጨት በሰውነቱ ተሸክሞ ከእግዚአብሔር አብ ቁጣ፤ ከሞትና ከሐጥያት አድኖኗል። እዚህ ጋር ግን አያበቃም። ይህ ግማሽ እውነት ነውና። ስለዚህ እውነተኛ ደህንነት ግን “የልጁን መልክ” በመምሰል መክበርን ገንዘቡ ማድረግ አለበት። የመጨረሻ ግባችን ልጆች መሆን ነው (1 ዮሐ 3:1-5) መዳናችንን ከሌሎች ፍጥረታት መዋጀት የሚለየው መዳናችን የእግዚአብሔርን ልጅ ኢየሱስን መምሰላችን ነው። የእግዚአብሔር ቤተሰቦች በመሆን ከመለኮት ባሕርይው እንድንካፈል ተዋጅተናል (2 Pet 1:2; John 1:2-3)። ይህ ከፍ ብዬ ወደ ጀመርኩት ነጥብ ያመራኛል። ይህም የመንፈስ ቅዱስ በበዓለ ሃምሳ ተልኮ መምጣቱና በልባችን ማደሪያ መሥራቱ አላማው በግል የልጁን መልክ እንድንመስል እንዲሁም እንደ አካል ደግሞ እግዚአብሔር የሚኖርበት ሕያው ቤተ-መቅደስ ሆነን እንድንሰራ ነው (there is an eschatological progression of sonship as well as temple imagery) መንፈሱንም ‘የክርስቶስ መንፈስ’ በማለት የመንፈስ ቅዱስን ተልዕኮና ሥራ ይገልጽልናል። ይህ መንፈስ በስሉሱ አምላክ የውስጥ ሕይወት ውስጥ የሚሰርጽ እንደመሆኑ መጠን ለአካሉ የሚመጥነውን ሥራ ደግሞ በእኛም ሕይወት ይሰራል። ከዚህ የተነሳ መዳናችንን ስሉስ በሆነ መልክ በኤፌሶን ተገልጧል። ይህም የምንቀርብበት መንገዱም ሆነ ፍጻሜያችን በስሉሱ አምላክ የተቀመረ ነው። ስለ አቀራረባችን ሲያሳየን “በእርሱ [በክርስቶስ] ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና (Ephesians 2:18)” የምንቀርበው በአብ ፊት ሲሆን መንገዱ ደግሞ በወልድ ሥራ አማካይነት በአንዱ በመንፈስ ቅዱስ በኩል ነው (depicted in highly in Trinitarian terms but reverse order. THe father revealed himself to us, through Christ, by the holy Spirit. We experience this revelation by the Spirit, through Christ.)
ከዚህ የተነሳ የመንፈስ ቅዱስን ፕሮጄክት ሐዋርያው ሲነገርን “
- እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን። (2 Corinthians 3:18)
በውስጣችን ያለው የልጅነታችን መንፈስ ሊመጣ ላለው ርስት መያዣ መሆኑንም መጽሐፍ ቅዱስ ያሳየናል (በዚህ ምክኒያት ሐዋርያው መንፈስ ቅዱስን የርስታችን መያዣ/አራቦን የሚል ሥያሜ ይሰጠዋል ‘ἀρραβὼν ኤፌ. 1:14’)
ስለዚህ መጽሀፍ ቅዱስ በልጁ በኩል የተገለጠውን ደህንነት ‘የማስመለጥ’ ተልዕኮ ብቻ ሳይሆን (ምንም እንኳ ይህ ትልቁን ሥፍራ የሚይዝ እውነት ቢሆንም) ‘የመለወጥ’ ተልዕኮን ይጨምራል። ይህንን ተልዕኮ ወልድ ይዞ ተገልጧል። ለማጠቃለል በዮሐንስ 17 ላይ የወልድ ተልዕኮ፦
- የአብን ሕልውና ወልድ ለደ/መዝሙርቱ ገልጧል
- ከዓለም ለሰጠኸኝ ሰዎች ስምህን ገለጥሁላቸው። የአንተ ነበሩ ለእኔም ሰጠሃቸው ዮሐ 17:6
- እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህን አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ። John 17:26 (AMHB)
- ሕይወትን የሚሰጡ ቃሎች ከአብ ዘንድ ወደ ደቀ/መዛሙርቱ፤ (ከደቀመዛሙርቱ ወደ እኛ ቀርቧል)
- ቃልህንም ጠብቀዋል። የሰጠኸኝ ሁሉ ከአንተ እንደ ሆነ አሁን ያውቃሉ፤ የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ከአንተም ዘንድ እንደ ወጣሁ በእውነት አወቁ፥ አንተም እንደ ላክኸኝ አመኑ። John 17:7–8 (AMHB)
- በእውነትህ ቀድሳቸው፤ ቃልህ እውነት ነው። John 17:17 (AMHB)
- ከአብ ዘንድ ያለውን የወልድን ክብር በውስጣችን በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት እንካፈላለን (የመንፈስ ቅዱስ አንዱ ሚና ከክርስቶስ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ ማሰር ነው፤ በዚሁ ወንጌል በዮሐ 14 ላይ ይህንን ሚና አብና ወልድ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ከአማኙ ጋር እራት በመብላት ተገልጧል)
- ሁሉም አንድ ይሆኑ ዘንድ፥ ከቃላቸው የተነሣ በእኔ ስለሚያምኑ ደግሞ እንጂ ስለ እነዚህ ብቻ አልለምንም፤ አንተ እንደ ላክኸኝ ዓለም ያምን ዘንድ፥ አንተ፥ አባት ሆይ፥ በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ እለምናለሁ። እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል። John 17:20–23 (AMHB)
ስለዚህ መዳን እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። እግዚአብሔር ሲያድነን ከጠላትነትና ከሃጥያተኛነት ወደ ክብርና ወደ ልጅነት አምጥቶናል። ከአባቱ ጋር የመለኮት ክብር ገንዘቡ ሆኖ ሲኖር ከነበረበት ልዕልና ክብሩን ወደ ማታውቅ ወደዚህች ዓለም በመምጣት ራሱን አዋረደ (John 17:19, Phil 2:9-11) ። የመጣው የአባቱን ፈቃድ ለመፈጸም ነበር። ሆኖም ግን በዚህ በተዋረደ የመስቀል ሞት በኩል የአባቱን ፈቃድ በመፈጸሙ አብን አከበረ። አብ ደግሞ ወልድን ያለልክ አከበረው፤ በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ ሥልጣንን ሰጠው፤ ከብሮ እኛንም አከበረን። በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ ደግሞ ክብር ገንዘባቸው ሆነ!
- እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ፤ አሁንም፥ አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር በአንተ ዘንድ በነበረኝ ክብር አንተ በራስህ ዘንድ አክብረኝ።
ስለዚህ እኛም በባህሪያችን ሞት የተገባን፤ በሐጥያት የተለወስን ጸያፍ ሰዎች፤ ከልጁ ሕይወት/ደም ክቡርነት የተነሳ ከዚህ ስሉስ ሕይወት እንድንካፈል (በእኔ እንዳለህ እኔም በአንተ፥ እነርሱ ደግሞ በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ) በር ተከፈተልን። መዳን ሕይወት ነው። ሕይወትንም ማግኘት መዳን ነው። መዳን እግዚአብሔርን ማወቅ ነው፡፡ ይህም የዘላለም ሕይወት ነው። ለምን ይሆን ወደ መንግሥቱ ገብተን፤ ከእልፍኙ ውስጥ አብረን ታድመን ከስሉሱ ንጉስ ገበታ የምንጋራው? የማይጠገበውን የልጁን ክብር እናይ ዘንድ ነው። ይህም ክብር ወልድ በአብ መወደዱ ነው። ይህ መወደድ ለወልድ ክብሩ ነው (አባት ሆይ፥ ዓለም ሳይፈጠር ስለ ወደድኸኝ)። ከዚህ ገበታ የሚፈረፈርውን የፍቅር ፍርፋሪ ብንለቅም አቤት እንዴት ታላቅ ክብር ይሆን!? ነገር ግን አብ ያፈሰሰልንን ፍቅር ተመልከቱ (1ዮሐ 3:1-5)! ልጆች አደረገን። ይህም ልጁ በሚወደድበት ፍቅር ተወደድን! ይህንን ፍቅር ተመልካቾች ብቻ ሳንሆን ነገር ግን ከዚህም ፍቅር ተካፋዮች እንድንሆን አበቃን! (እኔንም የወደድህባት ፍቅር በእነርሱ እንድትሆን እኔም በእነርሱ፥ ስምህን አስታወቅኋቸው አስታውቃቸውማለሁ) ፍቅር እንደዚህ ነው! እኛ እንደወደድ ሳይሆን አብ እንደወደደንና ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከልን ነው። ለምን ወደ መንግሥተ ሰማይ መግባት ይናፍቀናል? አንዳንዶች እንደሚሉት ወርቅ ስላለ ነው? እረፍት ስላለ ነው? ወይስ ለመዘመር ነው? የመጠቀ ዕይታ አለን፤ የእግዚአብሔር ልጅ እንዲህ ብሎናል፡-
- የሰጠኸኝ ክብሬን እንዲያዩ እኔ ባለሁበት የሰጠኸኝ እነርሱ ደግሞ ከእኔ ጋር ይሆኑ ዘንድ እወዳለሁ።
ማራናታ እንበል! ወደ መዳናችን ለመግባት እንዘጋጅ። ስንሔድ የልጁን ክብር እናያለንና! መዳን ማለት ስሉሱን አምላክ በማወቅ ወደ ሚገኝ ፍጹም አንድነት መድረስ ነው። ይህንን ዳርቻ በልጅነት ይገልጸዋል። ልጆች ሆነን እንከብራለን። ሆኖም ግን ያ ክብር አሁን በውስጣችን እንዲኖር ከሰጠን በመንፈሱና በሐዋርያቱ አማካይነት ትቶልን በሔደው ቃሎቹ መቅመስ ጀምረናል።
የሚቀጥለው ርዕስ፡ ሦስት ገጽታ ያለው መዳናችን
፪
ሦስት ገጽታ ያለው መዳናችን
ከላይ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድነት ሁለት እይታዎችን ገንዘቡ እንዳደረገ በፈረስ ግልቢያ ይመስል ፈጠን ፈጠን ብለን አይተናል። እነዚህም፤ ከእኛ ዕይታ አንጻር፤ መዳን እንደ ሁለት ጫፎች መስለነው ‘ከየትና ወዴት’ ብለናቸዋል። በጉዞ ላይ እንዳለ የእሥራኤል ሕዝብ፤ ለቀውት የመጡት ግብጽ ከኋላቸው፤ ከፊታቸው ደግሞ ሊገቡባት ያለችው ማርና ወተት የምታፈሰው የተስፋይቱ ምድር እንደነበረች፤ እኛም መዳናችን ከኋላ የተረፍንበት፤ ደግሞም ከፊት የምንወርሰው ሐብታችን ነው። ይህም መዳናችን አሉታዊና አዎንታዊ ገጽታ አለው ማለት ነው። አሉታዊ ያልነው መዳን መትረፍን ያመለክታልና ነው፤ ለሐጥያታችን ቅን ፍርድ ከሆነው ከእግዚአብሔር ቁጣ የተረፍን ሕዝቦች ነንና (ትሩፋን)። እግዚአብሔር አምላካችን እዚህ ጋር ቢተወን ኖሮ ጻድቅ፤ መልካምነቱም ወደር የለሽ በሆን ነበር። ምክኒያቱም ዝም ቢለን ኖሮ እንደ ሶዶምና እንደ ጎሞራ የምንሆነውን እኛን በጸጋው አንድያ ልጁን በመላክ አተረፈን። ግን የአምላካችንና የአዳኛችን ታላቅ ምህረት ሲገለጥ አትርፎ ቢተወን ኖሮ የሚበቃንን እኛን ‘ልጆቹ እንሆን ዘንድ አስቦ ወለደን። ይህንን ነው ‘ወዴት በሚለው ያካተትነው። ይህንን ታላቅ እውነት ቀለል አድርጎ ለማስተዋወቅ ያህል ብቻ እንጂ መዳን ሌላ ሦስተኛ ገጽታም አለው።
መዳን ሁሉን የሚዳሥ ሠፊ ፕሮጄክት ነው
መጽሀፍ ቅዱስ ስለመዳናችን ሲናገር አንድቀን በሕይወታችን የተጠናቀቀ ፕሮጀክት እንደሆን አያቀርበውም። ለምሳሌ ያህል አማኞች ብዙውን ጊዜ እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። በተለይ ደግሞ ይህንን ስህተት መስራት የማይገባን አገልጋዮችን ጨምሮ “አሁን ስለሚያደርግልኝ ከማመሰገነው ይልቅ፤ ከሁሉ በላይ ስለመዳኔ አመሰግነዋለሁ” ስንል እንደመጣለን! በግርድፉ ስታዩት እውነት ይመስላል “የቀን ውሎ ሥራ…የደሞዝ ጭማሬ…ልጆች…ትዳር…ሐዘኔ..ደስታዬ…መከራዬ..ስኬቴ.. ከመዳኔ ጋር ምን አገኛነው?” ስለዚህ ይህ አባብል “ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ስለመዳኔ ተመስገን” ባይ ይመስላል። በርግጥ ይህ አባባል ሊበረታታ የሚገባና እውነት ነው። እውነትነቱ ግን በከፊል ብቻ ነው። በተጨማሪ ግን እንደምታው ያልታሰበ ጎጂ ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ መዘዝ አለው። ይህ አነጋገር በመጀመሪያ መዳን ያኔ ያመንን ቀን ብቻ የሆነ ክዋኔ እደሆን የአማኙን መረዳት ያሳያል። ሁለተኛ አሁን በአማኙ የሚሆነው ከፍታና ዝቅታ ከመዳኑ ጋር እንብዛ ግኙነት እንዳለውም አያሳይም። አማኙ ከእግዚአብሔር የሚቀበለው ደስታ ይሁን መከራ ከመዳኑ ጋር ምንም ግንኙነት አለው? የአሁኑ ገጠመኝ፤ የሥራ በር መከፈት…ወዘተ…ከመዳናችን ጋር ግንኙነት የለውም? ስለዚህ ይህ አነጋገር ጠለቅ ብለን ስናየው የቅርቡን ብቻ የሚያይ ይመስላል። ሦስተኛ፤ በአንድ ቀን መዳናችንና በአሁን የለውጥ ሒደታችን መካከል ረጅም ገደል በአማኙ ሐሳብ ውስጥ እንዳለም ይጦቁማል። ከዚህ ቀጥሎ እንደምንመለከተው ይህ አነጋገር መዳናችን በጣም ተራ በሚመስሉ ነገሮች ውስጥ ዕለት ዕለት እየሰራ መሆኑን አያስተውልም። እዚህ ጋር ይህችን ነገር-ቀመስ አነጋገሬን ልተውና ሁልጊዜም እንደማደርገው ወደ ቅዱስ ቃል ትንታኔ ውስጥ እንግባ። ከዚያ ወደዚህ ወደ ጀመርነው ሐሳብ እነመለስና እንዳኛለን።
ድነናል፤ እንድናለን ደግሞ እየዳንን ነው!
ከዚህ ቀጥሎ እባካችሁ “መዳን” የሚለውን ቃል አጠቃቀም አንባቢዬ እንዲያስተውሉ እመክራለሁ፦
- ድነናል (ኤፌ 2፡ 8-10)፦ “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም። እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ይህ ክፍል የሚያስገነዝበን መዳናችን አንድቀን የተከናወነ ነው። ሃላፊ ግስ ነው። ያድናችኋል ወይም እያዳናችሁ አይልም ሆኖም ግን አድኗችኋል። (ነገር ግን አንባቢው ቀጥሎ ያለውን ያንብብ። ይህ አንድ ቀን የተከናወነው መዳን በአዲስ ፍጥረት በመምሰል- መመላለስ በሚለው ቃል ሒደታዊ እንደሆነም ይጦቁመናል)
- እንድናለን (ሮሜ 5:8–10.)፦ ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል። ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን። ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤
የሚገርመው እዚህ ጋር ሐዋርያው ስለ መታረቃችን ሲጽፍ እንታረቃለን አይልም። ክርስቶስ የተሰቀለ ዕለት በጥቅልና ያመንን ዕለት በግል ታርቀናል። ሰላምን ተቀብለናል። ወደ ቆምንበት ጸጋ መቅረብ ችለናል። ሆኖም ግን ሐዋርያው መዳናችን ገና ያልተጠናቀቀ ፕሮጄክት እንደሆን ሲጦቁመን ሁለት ጊዜ ደጋግሞ “ከቁጣው እንድናለን…በሕይወቱ እንድናለን” ይለናል። ። ስለዚህ አሁን ብንታረቅም፤ አሁን ብንድንም ነገርን ገና በሙላት እንድናለን። (ተጨማሪ፡ 1ተሰ 5:6-8፤ 1ጴጥ 1:3-5) በተለይ ጴጥሮስ መዳናችንን “በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ” በማለት መዳናችን ወደ ፊት የሚከናወን ጭምር እንደሆን ያስረዳናል።
- እየዳንን ነው (1ቆሮ 1:18)፡የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን (በቁሙ ብተሮጉመው ‘ግን እየዳንን ላለን ለእኛ’– τοῖς δὲ σῳζομένοις ἡμῖν δύναμις θεοῦ ἐστιν) ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና”
- እዚህ ጋር ሐዋርያው ለዳኑት ግን የእግዚአብሔር ሃይል ነው ቢል በርግጥ እውነት ነበር። ነገር ግን ለማያምኑ (አሁን የመስቀሉ ቃል) ሞኝነት እንደሆነ አሁን ደግሞ እየዳኑ ላሉት ግን ሐይል ነው። ንፅፅሩ አሁን በማያምኑና አሁን በሚያምኑ ሰዎች መካከል ነው። እነዚህ የሚያምኑትን ሰዎች ጳውሎስ ‘ለሚድኑት’ ይላቸዋል። እዚህ ጋር በተጨማሪ ልናስተውል የሚገባው ነገር የመዳናችንም ሂደት ያ ያዳነን የመስቀሉ ቃል እንደሆነም ጭምር ነው። ያዳነን የወንጌል ቃል፤ አሁን የሚያድነን ደግሞም አንድ ቀን የሚያድነን ቃል ነው። ይህንን በ ዚሁ መጽሀፍ መጨረሻ ላይ በ 1ቆሮ 15፡1 ላይ (ወንድሞች ሆይ፥ የሰበክሁላችሁን ደግሞም የተቀበላችሁትን በእርሱም ደግሞ የቆማችሁበትን በእርሱም ደግሞ የምትድኑበትን (σῴζεσθε -እየዳናችሁበት ያለውን) ወንጌል አሳስባችኋለሁ)። ያመንን ዕለት የዳነው በወንጌል እንደሆነ ሁሉ፤ ዛሬንም ዕለት ዕለት በመዳናችን የምናድገው በወንጌል ሲሆን አንድ ቀን ደግሞ በፊት ታላቅ መዳናችን ውስጥ የሚያስገባን ይሀው የወንጌል ቃል ነው። የመድዳን ፕሮጀችት አንድ ወጥ ነው። ሒደቱም ሆነ ፍጻሜው በወንጌል የሚካሔድ ነው
ከብዙ የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎች መካከል እንደ ናሙና አድርጌ ከላይ የጠቀስኳቸው ጥቅሶች እንደሚያመልከቱን መዳን የሚለውን ቃል በሦስት ግዜያቶች (ግሦች) ያቀርበዋል። ከዚህ የተነሳ እነዚህ ሶስቱም እውነቶች ናቸው “በክርስቶስ ያመንን ቀን ድነናል፤ አሁን እለት እለት እየዳንን ነው፤ አንድ ቀን በሙላት እንድናለን” በእነዚህ ሶስት ገጽታዎች መካከል አበይት የሆኑ ቃሎችና ይህ የመዳን ሒደት ቀጣይነት እንዲኖረው ያደረጉት የወንጌሉ ቃልና መንፈስ ቅዱስ ናቸው። የወንጌል ቃል አድኖናል ደግሞ እያዳነን ነው። ባመንን ቀን በመንፈስ ቅዱስ ታትመናል ደግሞ አሁን እለት እለት መንፈስ ከሆነ ጌታ የልጁን መልክ እንድንመስል አሁን ከክብር ወደ ክብር ይለውጠናል። አሁን መንፈሱ የክርስቶስን ሙሽራ እያዘጋጃት ነው፤ ሆኖም ግን አንድ ቀን ክርስቶስ ሲመለስ ይህ መዳን ይፈጸማል።
እዚህ ጋር ትልቅ ማስጠንቀቂያ በፊታችን አለ! ይህም ወንጌልን ገንዘቡ ያላደረገ ለውጥ የመዳን ለውጥ አለመሆኑን ነው፤፡ አንዳንድ ጊዜ ቅዱሳንና መሪዎች እንዲህ ስንል እንደመጣለን “መዳናችን ጥሩ ነው…አሁን ግን የምንናገረው ስለመለወጥ ነው…” ይህ አባባል መዳንና መለወጥ ሁለት የተለያዩ ፕሮጀክቶች አድርጓቸዋል። ለማለት የተፈለገው ነገር ምድር ነው፤ እውነት ነው ብዙኋኑ ወንጌልን ሰምቷል። እሁድ እሁድ የሚታደመው ህዝብ ወንጌልን ሰምቷል፤ ግን መለወጥ የሚባለው የሕልም እንጀራ ሆኖብናል። ምን ብናደርግ ነው ሕዝባችን የለውጥ ሕይወት የሚለማመደው?” ስለዚህ ለለውጥ ሕይወት 10 መርሆች…የተዋጣ የቤተሰብነት መርሆች…የገንዘብ አያያዝና ብልጽግና መንገዶች፤ የሓይል መንገዶች፤ አራት የፍቅር መንገዶች…የጸሎት ህይወት መርህ…የቅድስና ህይወት መርህ…ወዘተ…እነዚህ ሁሉ መልካም ናቸው። ነገር ግን እነዚህ ሁሉ ከወንጌል የተነሳ የተደረጉ ለውጥ ካልሆኑ፤ ትልቅ የቆላስያስ ቤተክርስቲያንን መሰል-ስህተት ፈጽመናል። ወንጌል ሥር ሲሰድ የተገኘ ለውጥ ካልሆነ በስተቀር ክርስቲያናዊ ለውጥ አይደለም። (ስለዚህ ጉዳይ በወንጌል ማዕከላዊነት በጻፍሁት መጣጥፎች ላይ በሰፊው ዘርዝሬአለሁ። ለምሳሌ፡ ወንጌል በመጀመሪያይቱ ቤተክርስቲያን ሕይወት፡ የወንጌልን ንጽሕናና ቀዳሚነት አጥብቆ መያዝ) የሕይወት ለውጥ ያለው የመለኮት ሁሉ ሙላት በእርሱ ዘንድ ይኖር ዘንድ በወደደው በልጁ ውስጥ ብቻ ነው። ይህንን አባባል ሐዋርያው “የመለኮት ሁሉ ሙላት…ወይም እንደ ክብሩ ባለጠግነት መጠን…በሚሉ ቃላት እግዚአብሔር ለሕዝቡ ያዘጋጀው ሙላት በልጁ ውስጥ ብቻ መኖሩንና ያለ ልጁ መሰበክና መታወቅ እነዚህ የአማኙ ገንዘብ ሊሆኑ እንደማይችሉ ያሳያል- ኤፌ 3፡14-21። ለዚህማ ብዙ ጠቃሚ ይህንን ዓለም የማይሻገሩ ምክሮችንና በሰውን ሕይወት ላይ ተጸዕኖ የሚያመጡ ነገሮችማ አለምም እኮ አላት። ነገር ግን የአብ አላማ በውድ ልጁ፤ ልጁን እንድንመስል ነው። ይህ ነው እውነተኛ ለውጥ፦ ክርስቶስን መምሰል። ይህ ደግሞ የወንጌል ፍሬ ነው። ወንጌልን አማኙ ሲረዳና በሕይወቱ ሥር ሲሰድ የሚገለጥ ፍሬ ነው። ከዚህ የተነሳ እኛ ለውጥ የምንለው ሁሉ የወንጌል ፍሬዎች እንደሆን ለናሙና ያህል እነመልከት-፡
- “እንግዲህ እንደ ተወደዱ ልጆች እግዚአብሔርን የምትከተሉ ሁኑ፥ ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ በፍቅር ተመላለሱ” (ኤፌ. 5:1–2) ይህ ማለት በወንጌል የተገለጠው የክርስቶስ ተልዕኮ ለመዳናችንም ደግሞም በመዳናችን ከሕይወቱ ተካፋዮች እንድንሆን ምሳሌንም ሊተውልን ጭምር ነው። ይህንን ምሳሌ መከተል ልክ ልጅ አባቱን እንደሚመስል መለወጥ ነው። ስለዚህ በዚህ ምዕራፍ ክርስቶስን መምሰል ውጤቱ ምን ይመስላል?
- ለቅዱሳን እንደሚገባ ግን ዝሙትና ርኵሰት ሁሉ ወይም መመኘት በእናንተ ዘንድ ከቶ አይሰማ (ቁ.3)
- የሚያሳፍር ነገርም የስንፍና ንግግርም ወይም ዋዛ የማይገቡ ናቸውና አይሁኑ፥ (4)
- የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥9-11
- እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ
- በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ፤ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።
- ሚስቶች ሆይ፥ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁ ተገዙ፤
- ባሎች ሆይ፥ ክርስቶስ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ወደዳት ሚስቶቻችሁን ውደዱ፤ በውኃ መታጠብና ከቃሉ ጋር አንጽቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ። ሆኖም ከእናንተ ደግሞ እያንዳንዱ የገዛ ሚስቱን እንዲህ እንደ ራሱ አድርጎ ይውደዳት፥ ሚስቱም ባልዋን ትፍራ።
- ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና።
- ባሪያዎች ሆይ፥ ለክርስቶስ እንደምትታዘዙ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ በልባችሁ ቅንነት በሥጋ ጌቶቻችሁ ለሆኑ ታዘዙ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንደሚያደርጉ እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች እንጂ ለሰው ደስ እንደምታሰኙ ለታይታ የምትገዙ አትሁኑ።
- እናንተም ጌቶች ሆይ፥ ዛቻውን ትታችሁ እንዲሁ አድርጉላቸው፥ በእነርሱና በእናንተ ላይ የሚገዛው ጌታ በሰማይ እንዳለ ለሰው ፊትም እንዳያደላ ታውቃላችሁና።
- በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ። የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ።
ወንጌል በአማኙ ሕይወት ሥር ሲሰድ ከላይ እንደተመከትነው የሚዳሥሠው የሰውን ሁለንተና ነው። ከነዚህ መካከል (ከኤፌ 5:1-6፡12) ሥነ-ምግባራዊ ለውጥን ገንዘቡ ያደረገ ነው፤ በጥበብ መመላለስን፤ በመዝሙርና በቅኔ ማወደስን ገንዘቡ ያደረገ ነው፤ የባልና የሚስት፤ የ ወላጆችና የልጆችን፤ የአሠሪና የሰራተኞችን ግንኙነት ይዳስሳል። የምለው ይህንን ነው፤ እነዚህ ለውጦች ግን “ክርስቶስም ደግሞ እንደ ወደዳችሁ ለእግዚአብሔርም የመዓዛ ሽታ የሚሆንን መባንና መሥዋዕትን አድርጎ ስለ እናንተ ራሱን አሳልፎ እንደ ሰጠ” የሚለው የወንጌል እውነት ይከተላሉ እንጂ አይቀድሙም። አማኙ የመረዳት ብልጽግና በመንፈስ ቅዱስ ሲያገኝ የሚሆኑ ነገሮች ናቸው። (በተጨማሪ እነዚህን ለናሙና ያንብቡ ፊል 2፡ 2-8፤ ሮሜ 15፡ 2-7) ስለዚህ የምንም ለውጥ ሒደት ብንናገር በመጀመሪያ የወንጌል እውነት ሥር ከተመሰረተ በኋላ መሆን አለበት። በርግጥ ለውጥ ማለት ክርስቶስ ስለ እኛ የሆነውን መምሰል ነው (there is a mirroring of relationship) ካልሆነ አትንካ አትቅመስ የሚል ከንቱ የሰው ሥርዓቶች ብቻ ናቸው፡፤ እነዚህም በተግባር ሲደረጉ የሚጠፉና ለሥጋ ልቅነት አንዳች ፋይዳ የሌላቸው መርሆች ናቸው። ይህ በተለይ ለእኛ ለሰባኪዎች ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው። የለውጥ ስብከት በፊት መቅደም ያለበት የወንጌል እውነት ነው። ኢየሱስ ማነው? ተልዕኮውስ ማንድር ነው? የስውን ልጅ ማን ይሊታል? ከዚህ አንጻር ስንመለከት የለውጥ ሕይወት የወንጌል እንደምታ ነው። ወንጌል የሐይል ቃል እንጂ ባድ ንግግር አይደለም፡፤ ሐይል ከሆነ ዘንዳ በአማኙ ውስጥ ሰርጾ መስራት የሚችል ጉልበት ነው።
የወንጌሉ እውነት(The description of the Gospel) |
የወንጌል እንደምታ/ትዕዛዝ( the Implication/ Imperative of the Gospel) |
ገላትያ ምዕራፍ 1 እስከ 4 ወንድሞች ሆይ ፣ የሰበክሁላችሁ ወንጌል ሰው ሰራሽ አለመሆኑን እንድታውቁ እፈልጋለሁ። (1፥11) | ገላትያ ምዕራፍ 5 እና 6 ክርስቶስ ነጻ ያወጣን በነጻነት እንድንኖር ነው ። ስለዚህ ጸንታችሁ ቁሙ ፤ ዳግመኛ በባርነት ቀንበር አትጠመዱ። |
ኤፌሶን ምዕራፍ 1 እስከ 3 በሰማያዊ ስፍራ፣ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ በክርስቶስ የባረከን የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ | ኤፌሶን ምዕራፍ4 እስከ6 1 እንግዲህ በጌታ እስረኛ የሆንሁ እኔ፣ ለተቀበላችሁት ጥሪ የሚገባ ኑሮ ትኖሩ ዘንድ እለምናችኋሁ። |
ቆላስይስ ምዕራፍ 1 እስከ 2 እርሱ የማይታየው አምላክ አምሳል ነው፤ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኩር ነው፤ እኛም እያንዳንዱን ሰው በክርስቶስ ፍጹም አድርገን ማቅረብ እንችል ዘንድ፣ ሰውን ሁሉ በጥበብ ሁሉ እየመከርንና እያስተማርን እርሱን እንሰብካለን ፤ እኔም በብርታት በውስጤ በሚሰራው በእርሱ ኃይል ሁሉ እታገላለሁ፤ ለዚህ ዐላማ እጥራለሁ። | ቆላስይስ ምዕራፍ 3 እስከ 4 እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሳችሁ ፣ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ በተቀመጠበት በላይ ያሉ ነገሮችን እሹ፣ |
1 ቆሮንቶስ ምዕራፍ 1 እስከ 2የመስቀሉ ኃይል ለሚጠፉ ሞኝነት ነው፤ ለእኛ ለምንድነው ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነው ፤ | 1 ቆሮንቶስ ምዕራፍ 3 እና ከዚአ በህዋላ ያሉት ፣ጳውሎስ የቆሮንጦስ ሰዎች የጻፉለትን ጥያቄዎችና ጉዳዮች ሁሉ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ምዕራፎች በአቀረበው ወንጌል መሠረት መመለስና መፍታት ይጀምራል |
ሮሜ 1፥16 -11በሮም ለምትኖሩ ፣ ለእናንተም ወንጌልን ለመስበክ የምጓጓው ለዚህ ነው። በወንጌል አላፍርም፤ ምክንያቱም ለሚያምን ሁሉ ለድነት የሚሆን የእግዚአብሔር ኃይልነው፤ በመጀመሪያ ለአይሁድ ፣ ቀጥሎም ለአሕዛብ ነው። | ሮሜ 12 -16እንግዲህ ወንድሞች ሆይ ፤ ሰውነታችሁን ቅዱስና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕያው መስዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ ፤ ይሕም እንደባለ አእምሮ የምታቀርቡት አምልኮአችሁ ነው። |
በልማድ መዳን የሚለውን ቃል ስንጠቀም በጠባቡና በመጀመሪያው ገጽታ ነው። ይህም ባመንን ዕለት አንድ ቀን የተከናወነ ነው። ሆኖም ግን ሊሰመርበት የሚገባው ይህ ባመንን እለት የሆነው የመዳን ሙሉ ገጽታ አይደለም። እውነት ነው፤ የማይደገሙ አንድ ጊዜ የሆነ በመዳን ሥር የሚካተቱ ክንዋኔዎች ተፈጽመዋል። ሆኖም ግን እነዚህ መዳን የሚለውን እውነታ ሙሉ በሙሉ መግለጫዎች አይደሉም። ባመንን እለት ምን ሆነ? እግዚአብሔር ይመስገን አዳነን! መዳናችን ግን በዙ ገጽታ ባላቸውና ብዙ እውነታዎችን በሚያንጸባርቁ ዘይቤያዊ አነጋገሮች ተገልጦአል። ከእነዚህ መካከል ጥቂቶቹ ይህንን ይመስላሉ፦ መጽደቅ፤ ጥሪ፤ ቅድስና፤ ዳግም ልደት፤ ልጅነት፤ ዕርቅ፤ ትድግና፤ መዋጀት፤ ቤዛነት፤ ሥርየት፤ ሰላም፤ መግባት፤ መክበር ወዘተ… እነዚህ ሁሉና እነዚህን የመሳሰሉ የአንዱ መዳን ለሚለው እውነታ ገጽታዎች እንጂ ምትኮች አይደሉም። ሐዋርያው ጳውሎስ ለምሳሌ እነዚህ የአንዱ መዳን ገጽታዎች እንደሆኑ ሲያሳየን “ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤ አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።” በተጨማሪ ያህል ከእነዚህ የአንዱ መዳን ገጽታዎች ከሆኑት ብዙ ዘይቤያዊ አነጋገሮች መካከል እንደ ናሙና አድርጌ “የጽድቅን ብያኔ ስለመቀበል” (justification) እንመልከት፡-
- የጽድቅን ብያኔ ተቀበልን (Justification)፡- በእኛ ላይ የነበረው ክስ፤ ኩነኔና ፍርድ ተሠረዘ ማለታችን ነው። በሕያው እግዚአብሔር ፊት ወንጀለኛ የሚል ሥያሜ ተነሳልን። የሰውን ፊት አይቶ በማያዳላው፤ በጻድቅ ፈራጅ፤ በዓለሙ ሁሉ አምላክና ዳኛ ፍርድ ቤት ውስጥ ጉዳያችን በንጉስ ማህተብ ተዘጋ። ከእንግዲህ ወዲህ ይህ የንጉሰ ነገስት ፍርድ ቤት በልጁ ደም ስርየት ምክኒያት ወንጀልህ እንዳልነበረ ተሰርዟል። በአንተ(ቺ)(እርሶ) ላይ ያለው ሰነድ ስለ በደል የሚናገረው ጉዳይ የለም። (criminal record in this country can be cleared if proven innocence of the crime)። ይህ ባመንን እለት እግዚብሔር አብ በእኛ ፈንታ ከፈሰሰው ከክርስቶስ ደም የተነሳ የተቀበልነው ብያኔ ነው። (ከሐጥያታችን የተነሳ በቁጣው ፍርድ ምክኒያት የእኛ ደም መፍሰስ ቅን ፍርድ ሆኖ ሳለ ከታላቅ ምሕረቱ የተነሳ የእርሱ ንጹህ ደም ፈስሶ እኛ በነጻ ተለቀቅን) ይህ የመዳናችን አንድ ገጽታ ነው። ለምሳሌ
- እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ፤ 2 በእርሱም ደግሞ ወደ ቆምንበት ወደዚህ ጸጋ በእምነት መግባትን አግኝተናል፤ በእግዚአብሔር ክብርም ተስፋ እንመካለን።
- እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው (የጽድቅ ብያኔ ነው)፤ ልዩነት የለምና፤ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ(የጽድቅ ብያኔ ይቀበላሉ)። እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ Ro 3:22–25.
- ተጨማሪ፦ Rom. 5:17; Rom 3:21; 9:30; 10:3–10; 2 Cor. 5:21; Phil. 3:9
ስለዚህ መዳን ማለት ሁሉን የሚጠቀልል፤ እግዚአብሔር በልጁ አምሳል ዳግም ለፈጠራቸውና ለጥቅል ፍጥረቱ የተዘጋጀው ታላቅ ፕሮጀችት ነው ማለት ነው። ሆኖም ግን ምንም እንኳ መዳናችን አሁን እየሰራና ወደ ፊት የሚገልጥ ቢሆንም አንዳንድ የመዳን በረከቶች ግን ዳግም ላይደገሙ የተከናወኑ ናቸው። ለምሳሌ ያህል ሲያድነን ከጨለማ ወደ ብርሃን፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሸጋግረናል። በዚህ ገጽታው ከሆነ መዳናችን እለት እለት እየሆነ አይደለም። ጌታን በየሳምንቱ አንቀበልም። አንድ ቀን አምነን የጌታ ሆነናል። ይህንን ነው በመግቢያዬ ላይ የገለጥኩት። ብዙ ጊዜ አማኞች መዳን የሚለውን በዚህ ብቻ ወስነው በጠባቡ ይመለከቱታል። ሆኖም ግን መንፈስ ቅዱስ በሕይወታችን በሥራ ላይ ነው። ሁሉ ነገር ተያይዞ (ሁሉ ነገር!) የሚሰራው ለአንድ ግብ ነው። የልጁን መልክ እንድንመስል እየተሰራን ነው። ይህም ሒደት መጽሀፍ ቅዱሳችን መዳን በሚለው ሰፊ ፕሮጀክት ላይ ያጠቃልለዋል እንጂ ሌላ ተጨማሪ ተልዕኮ አይደለም። ይህ ሒደት (process of sanctification) ከመጽደቃችንና ከመታረቃችን የቀጠለ እንጂ ሌላ አዲስ ሥራ አይደለም። ግባችንም በሙላት ልጆች መሆን ነው፤ ይህንን ዓላማ ክብር ይለዋል። ወደ ክብሩ ተጠርተናል፡ ልክ ለወልድ በአባቱ መወደዱ ክብሩ እንደሆን ክብራችንም ልጆች መሆን ነው።
ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ…
በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን። በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን። በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ። በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት። ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን። በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው። እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን። ይኸውም፥ በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው። እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤ እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል። Ephesians 1:3–14
ሐዋርያው ይህንን ደብዳቤ ለመጻፍ የተጠቀመበትን ቋንቋ አንባቢ የሆናችሁ ይህንን ማስተዋል ትችላላችሁ። በምዕራፍ አንድ ከቁጥር 3-14 ሲጽፍ ትንፋሽ አልወሰደም። በመሃከል ነጠላ ሰረዝ፤ ሁለት ነጥብ፤ አራት ነጥብ አልተጠቀመም። ይህ ማለት ከቁጥር ሦስት ጀምሮ እስከ ቁጥር አሥራ አራት ድረስ አንድ ረጅም ዓረፍተ-ነገር ነው። ሐዋርያው እግዚአብሔር በክርስቶስ በኩል የገለጠልንን መዳን ታላቅ መሆኑን በማስገንዘብ ልባዊ ምሥጋናውን ሲገልጥ እረፍት ሊያደርግ አልወደደም።
- የተባረክነው በሚወደው ልጁ በክርስቶስ ነው፦ በዚህች አጭር አረፍተ ነገር ውስጥ ከ 11 ጊዜ በላይ በመደጋገም ሁሉን ነገር የተቀበልነው “በክርስቶስ/ በእርሱ/በሚወደው” መሆኑን ይነግረናል። ይህም መዳናችን ከክርስቶስ ጋር አንድ መሆናችን ነው። እርሱ ሐጥያታችንን በመሸከም እኛን መሰለ፤ እኛ ደግሞ የሐጥያትን ሥርየት ካስገኘልን በኋላ እርሱን እንመስል ዘንድ።
- የባረከን የክርስቶስ አባት ነው፦ እዚህ ጋር አሁን አባት ብለን የምንጠራው አምላካችን በመጀመሪያ ደረጃ የወልድ አባት መሆኑን ያሳየናል። ለዚህ ነው ስለ ክርስቶስ ሲናገር “በሚወደው ልጁ” ሲል ስለ እኛ ግን “ለእርሱ ልጆች እንሆን ዘንድ አስቀድሞ ወሰነን” የሚለን። ክርስቶስ የዘላለም ልጅ ሲሆን እኛ ግን ልጆች እንሆን ዘንድ የተቀበለን ልጆች ነን (adopted sons)። ይህ የሐዋርያው የባረከንን የሚባርክበት ታላቅ ምክኒያት ነው። ከመዝሙረኛው ዳዊት አንሥቶ እስከ ክርስቶስ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን እንደጸሎት ቀመር አድርገው የሚጠቀሙበት ሐረግ አለ። ለምሳሌ ዳዊት የባረከውን አምላክ እየባረከ ሲዘምር “የልመናዬን ቃል ሰምቶኛልና እግዚአብሔር ይባረክ…ከዘላለም እስከ ዘላለም የእስራኤል አምላክ እግዚአሔር ይባረክ” መዝ. 28፡ 6 ፤ 31፡ 21፤ 41፡13፤ 119፡12 በተጨማሪ “ዳዊትም በጉባኤው ሁሉ ፊት እግዚአብሔርን ባረከ፤ ዳዊትም አለ። አቤቱ፥ የአባታችን የእስራኤል አምላክ ሆይ፥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ተባረክ” 1ዜና 29:10። ክርስቶስ በተገለጠበትም ዘመን አይሁድ፤ ከዚህ ተከትለው በዘወትር ጸሎታቸው መጀመሪያ “ባሩክ አታህ አዶናይ ኤሎሔኑ…ብሩክ ነህ አንተ ጌታ አምላካችን….” በማለት ባርኮታቸውን መዘርዘር ይጀምራሉ። ጳውሎስም ክርስቶስን በደማስቆ መንገድ ላይ ከመገናኘቱ በፊት ብዙ ጊዜ እንዲህ ብሎ ይጸልይ እንደነበር መገመት አዳጋች አይደለም። እዚህ ጋር ግን ሐዋርያው ጳውሎስ በልማዱ ላይ ሠበር ቃል ይከታል። ይህም ያ የአባቱ የአብርሃም አምላክ አዳናይ-ኤሎሔኑ (ጌታ-አምላክ) አሁን የሚታወቀውና በጸሎት የሚጠራው “አምላክ የጌታችን የክርስቶስ ኢየሱስ አባት ተብሎ ነው!” እዚህ ጋር ብዙ መሠረታዊና ጥልቅ እውነታዎች ተንጸባርቀዋል። በመጀመሪያ ዳዊትና አይሁድ ‘ጌታ’ ብለው ያህዌህን እንደጠሩት አሁን ይህንኑ ስም (ጌታ) ለኢየሱስ በማጎናጸፍ ክርስቶስ ከአባቱ ጋር በማዕረግ አንድ መሆኑን ያሳየናል (ከዘዳ 6:4 ጋር ያጣቅሱ)። ሁለተኛ በክርስቶስና በአብ መካከል ያለውን ግኑኝነት ያጎላል። ክርስቶስ የአብ ልጅ ነው። መዳን ማለት ደግሞ በሚወደው ልጅ አማካይነት ልጅ መሆን ነው።
- የተባረክነው በመንፈሳዊ በረከቶች ነው፡- እዚህ ጋር ሐዋርያው መንፈሳዊ ሲል ከቁሳዊ ነገር ጋር እያቃረነ እንዳለሆነ ሊሰመርበት ይገባል። ይህም የመዳን በረከት ቁሳዊ ሳይሆን መንፈሳዊ አድርጎ ማቅረብ ማለት ነው። ሆኖም ግን ይህ አስተሳሰብ የግሪኮች መንትያ አስተሳሰብ (dualism) እንጂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተሳሰብ አይደለም። ሐዋርያው ግን መንፈሳዊ ሲል፤ የበረከታችንን ምንጭ ለማመልከት ነው። ይህም ያገኘናቸው በረከቶች ከአሮጌው ሥርዓት የፈነጠቁ ሳይሆኑ ሁሉን ሊጠቀልል በወደደበት በልጁና የርስታችን መያዣ አድርጎ በሰጠን በመንፈሱ የታቀፈ በረከት እንደሆን ለማመልከት ነው። (እዚህ ጋር ወደ ረቀቀ የቃል አጠቃቀም ትንታኔ ውስጥ መግባት ለምትፈልጉ መንፈሳዊ ተብሎ የተተረጎመው ቃል ‘ፕኑሟቲካስ/πνευματικός’ ነው)
- የተባረክነው በመንፈሳዊ ሥፍራ ነው፦ ሲል አሁንም እነዚህን በረከቶች የተቀበልንበትን ልዕልና ለማመልከት እንጂ እነዚህ በረከቶቹ በመንፈሳዊ ዓለም ብቻ የተወሰኑ እንደሆን ለማመልከት አይደለም። ይህ ሥፍራ ጌታችን ወደ አባቱ ዘንድ ሲመለስ ጌታና ክርስቶስ ሆኖ የተሾመት ሥፍራ ነው። ስለዚህ ይህ ቃል የክርስቶስን ሹመት፤ በርሱ በኩል ወደ ተመረቀው አዲስ ሥርዓትና መሲሐዊ ዘመን መፈንጠቅ ያመለክታል (Inaugurated Eschatology)። ክርስቶስ አንድ ቀን የምንሆነውን ሁሉ አሁን በአብ ቀኝ እኛን ወክሎ ይዞልናል። እኛም መንፈሱን ስለተቀበልን ከክርስቶስ ጋር አንድ እንድንሆን ተጠምቀናል ያም በረከት ከመንፈሱ የተነሳ በመጠን መካፈል ጀምረናል። ያህዌህ በዘመን ፍጻሜ ሊያደርግ የወደደው አሁን ተመርቋል፤ ምንም እንኳ ይጠናቀቅ ዘንድ ግን ዳግም-ምጽዓቱን ገና ቢጠብቅም። ስለዚህ ይህ እውነታ (በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ) መዳናችን አሁን እውን እንደሆን ነገር ግን ገና ወደ ፊት ደግሞ በሙላት እንደሚገለጥ ያሳየናል።
- “በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።”
- የተባረክነው በሥሉሱ አምላክ አሰራር ነው፡- ከላይ እንዳየነው በዚህ ወጥ ረጅም ዓረፍተ-ነገር ውስጥ አዝማች መሰል ሐረጎችን ሶስት ጊዜ በመደጋገም ሐዋርያው በመዳናችን ውስጥ የእያንዳንዱን የስላሴ አካል ሚናና ዓላማ ይነግረናል (ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ…ቁ 6፤ 11ና 14 ላይ)። መዳናችን በስሉስ አምላክ አካላት የተቀመረ፤ የተቀነባበረና የሥሉሱን አምላክ ክብር የሚያንጸባርቅ ነው። በስሉስ አካላት መዳፍ የተቀረጽን ነን። አንዱ አምላክ አብ በወልድና በመንፈሱ የተዳሰሰ ስጦታ ተሰጥቶናል። ስለዚህ ስጦታው አምላካችንን እንድናውቅ ያደርገናል።
- አብ፦ ልጁን የሚመስሉ ንፁሃን ልጆች እንሆን ዘንድ እንደ በጎ አቀደ
- ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።
- በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን። “በውድ ልጁም እንዲያው የሰጠን የጸጋው ክብር ይመሰገን ዘንድ ይህን አደረገ”
- አብ፦ ልጁን የሚመስሉ ንፁሃን ልጆች እንሆን ዘንድ እንደ በጎ አቀደ
- ወልድ፡ በዘመን ፍጻሜ
- የሓጥያትን ይቅርታ የሚያስገኝ ቤዛነት፡ “በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት። “
- በወልድ አማካይነት የሐሳቡ ሚስጢር ተገለጠ፦ ጸጋውንም በጥበብና በአእምሮ ሁሉ አበዛልን። 9 በክርስቶስ ለማድረግ እንደ ወደደ እንደ አሳቡ፥ የፈቃዱን ምሥጢር አስታውቆናልና፤ በዘመን ፍጻሜ ይደረግ ዘንድ ያለው አሳቡም በሰማይና በምድር ያለውን ሁሉ በክርስቶስ ለመጠቅለል ነው።
- እንደ ፈቃዱ ምክር ሁሉን የሚሠራ እንደ እርሱ አሳብ፥ አስቀድመን የተወሰንን በክርስቶስ ደግሞ ርስትን ተቀበልን።
- ይኸውም፥ በክርስቶስ አስቀድመን ተስፋ ያደረግን እኛ ለክብሩ ምስጋና እንሆን ዘንድ ነው።
- መንፈስ ቅዱስ፡ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥(እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ )
- በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤
- እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ “ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል”
- የልጅነታችን ሦስት ገጻዎች፡
- በዘላለም (አብ)፦ ልጆች እንሆን ዘንድ ወደደ (አላማውም ቅዱሳን (ለእግዚአብሔር የተለየ)ና ነውር አልባ (በብሉይ ለመስዋእት የሚቀርቡ እንሥሣትን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል)፟
- በዘመን መጨረሻ (ወልድ)፡ ልጆች የሚያደርግን ሥራ ስላከናወነ በደሙ የልጅነት በር ተከፈተ።
- በወንጌል ቃል መስማት አማካይነት ባመንን ጊዜ (በመንፈስ ቅዱስ)፦ በመንፈስ ቅዱስ ማህተም በመታተትም ደግሞ ልጅነታችን እውን ሆነ። አባ አባት ብሎ የሚጮህ መንፈስን ተቀብለናል።
በአጭሩ የመዳናችን ግብ የእግዚአብሔርን ቤተሰቦች እንድንሆን ነው፤ ይህም ልጅነታችን ነው። ለመከለስ ያህል መዳናችን ሁለት ጫፎችና ሦስት ገጽታዎች እንዳሉት አይተናል። መዳናችን ከየትና ወዴት የሚሉ ጫፎች አሉት። ከዬት የሚለው ጥያቄ የሚያሳየን ባመንን ጊዜ አሮጌው ሰው ከነ ፍርዱ ተሽሮ አዲሱን ሰው መልበሳችንን (ይህም እግዚአብሔር አብ በወልድ ሥራ አማካይነት በመንፈስ ቅዱስ ማሕተም አትሞን የሓጥያትን ይቅርታ መቀበላችን) ሲሆን ወዴት የሚለው ደግሞ በዚሁ በአንዱ መንፈስ አማካይነት ዳግም ክርስቶስ ሁሉን ሊጠቀልል በሚገለጥበት ጊዜ ሙሉ በሙሉ እውን ወደ ሚሆነው ልጅነታችን ላይ ያነጣጥራል። ከዚህ የተንሳ መዳን ሦስት ገጽታ አለው። በአንድ ገጽታ ድነናል። በሌላ ገጽታ አሁን ዕለት ዕለት እየዳንን ነው። ደግሞ አንድ ቀን ልጁ ሲገልጥ በሙላት እንድናለን። ክብር ሁሉ ለሉሱ ጌታ ይሁን!
የሚቀጥለው ርዕስ፡ የመዳናችን ገጽታ በሁለት ዘመናት (ድነናል፤ ግን ገን ደግሞ እንድናለን – The already but not yet dimension)
፫
በሁለት እውነታዎች ተወጥሮ የተቃኘ መዳናችን
መዳናችን አሁን ተገልጧል…መዳናችን ገና በሙላት ይገለጣል!
እጮኛ…ሙሽራ…ታዳሚ!
“በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና” (2 ቆሮ 11:2)
“ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ። ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ” (ኤፌ 5:31–32)
- ከዚህ በኋላ በሰማይ። ሃሌ ሉያ፤ በዝሙትዋ ምድርን ያጠፋችይቱን ታላቂቱን ጋለሞታ ስለ ፈረደባት፥ የባሪያዎቹንም ደም ከእጅዋ ስለ ተበቀለ፥ ፍርዶቹ እውነትና ጽድቅ ናቸውና ማዳንና ክብር ኃይልም የአምላካችን ነው ብሎ ሲናገር እንደ ብዙ ሕዝብ ታላቅ ድምፅ ያለ ድምፅን ሰማሁ። Re 19:1–2.
- እንደ ብዙ ሕዝብም ድምፅ፥ እንደ ብዙ ውኃዎችም ድምፅ፥ እንደ ብርቱም ነጐድጓድ ድምፅ ያለ ድምፅ ሰማሁ እንዲህ ሲል። ሃሌ ሉያ፤ ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላካችን ነግሦአልና። የበጉ ሰርግ ስለ ደረሰ ሚስቱም ራስዋን ስላዘጋጀች ደስ ይበለን ሐሤትም እናድርግ ክብርንም ለእርሱ እናቅርብ። ያጌጠና የተጣራ ቀጭን የተልባ እግር ልብስ እንድትጐናጸፍ ተሰጥቶአታል። ቀጭኑ የተልባ እግር የቅዱሳን ጽድቅ ሥራ ነውና። እርሱም። ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው ብለህ ጻፍ አለኝ። ደግሞም። ይህ የእግዚአብሔር እውነተኛ ቃል ነው አለኝ። Re 19:6–9.
- “በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ። ሴቲቱም በቅዱሳን ደምና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት። ባየኋትም ጊዜ እጅግ ታላቅ ድንቅ አደነቅሁ” ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች። 2 በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤ 3 አሕዛብ ሁሉ ከዝሙትዋ ቍጣ ወይን ጠጅ የተነሳ ወድቀዋልና፥ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ የምድርም ነጋዴዎች ከቅምጥልነትዋ ኃይል የተነሳ ባለ ጠጋዎች ሆኑ ብሎ ጮኸ። 4 ከሰማይም ሌላ ድምፅ ሰማሁ እንዲህ ሲል። ሕዝቤ ሆይ፥ በኃጢአትዋ እንዳትተባበሩ ከመቅሠፍትዋም እንዳትቀበሉ ከእርስዋ ዘንድ ውጡ፤አንድም ብርቱ መልአክ ትልቅን ወፍጮ የሚመስልን ድንጋይ አንስቶ ወደ ባሕር ወረወረው እንዲህ ሲል። ታላቂቱ ከተማ ባቢሎን እንዲህ ተገፍታ ትወድቃለች ከእንግዲህም ወዲህ ከቶ አትገኝም”
- “አዲስ ሰማይንና አዲስ ምድርንም አየሁ፥ ፊተኛው ሰማይና ፊተኛይቱ ምድር አልፈዋልና፥ ባሕርም ወደ ፊት የለም። 2 ቅድስቲቱም ከተማ አዲሲቱ ኢየሩሳሌም፥ ለባልዋ እንደ ተሸለመች ሙሽራ ተዘጋጅታ፥ ከሰማይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስትወርድ አየሁ። 3 ታላቅም ድምፅ ከሰማይ። እነሆ፥ የእግዚአብሔር ድንኳን በሰዎች መካከል ነው ከእነርሱም ጋር ያድራል፥ እነርሱም ሕዝቡ ይሆናሉ እግዚአብሔርም እርሱ ራሱ ከእነርሱ ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል፤ 4 እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል፥ ሞትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ ኀዘንም ቢሆን ወይም ጩኸት ወይም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፥ የቀደመው ሥርዓት አልፎአልና ብሎ ሲናገር ሰማሁ። 5 በዙፋንም የተቀመጠው። እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ አለ። ለእኔም። እነዚህ ቃሎች የታመኑና እውነተኛዎች ናቸውና ጻፍ አለኝ። 6 አለኝም። ተፈጽሞአል። አልፋና ዖሜጋ፥ መጀመሪያውና መጨረሻው እኔ ነኝ። ለተጠማ ከሕይወት ውኃ ምንጭ እንዲያው እኔ እሰጣለሁ። ድል የሚነሣ ይህን ይወርሳል አምላክም እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል” Re 21:1–7
የተመረቀች መንግሥት፤ የተመረቀ ኪዳንና የተመረቀ መዳን!
- “ጌታ ጌታዬን ጠላቶችህን የእግርህ መረገጫ እስካደርግልህ ድረስ በቀኜ ተቀመጥ…” መዝ 110:1
- እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ ሊቀ ካህናት ሊሆን ራሱን አላከበረም ነገር ግን። አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ ያለው እርሱ ነው፤ 6 እንደዚህም በሌላ ስፍራ ደግሞ። አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ይላል። 8 ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤ ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው። (Hebrews 5:5–6)
- ድነናል (Eph 2:8) ነገር ግን ገና ደግሞ እንድናለን (Rom. 5:9)
- ተቀድሰናል (1Cor 6:11) ነገር ግን ገና ደግሞ እንቀደሳለን (1Thess. 5:23-24)
- እንደ ልጆች ተቀብሎናል (Rom 8:15), ነገር ግን ገና ደግሞ ልጆች እንሆናለን (Rom 8:23)
- አዲሱን ሰው ለብሰናል (Col. 3:9-11), ነገር ግን ገና ደግሞ አዲሱን ሰው እንለብሳለን (Eph. 4:21-24)
- ተዋጅተናል (Eph. 1:7) ነገር ግን ገና ደግሞ እንዋጃለን (Rom 8:23)
ቅኝታችን ታድያ ምን ይመስላል?
ክራር-ነክ ሙዚቃ መሳሪያዎች በየጊዜው ይቃኛሉ። ይህም በሁለት ጥግ እያንዳንዱ ክሮች ትክክለኛ ቅኝታቸውን እስኪይዙ ድረስ መወጠር አለባቸው። አሊያ ዜማቸው ጥዑም አለመሆን ብቻ ሳይሆን የዜማን መርህ ስለሚጣረስ ዜማ መደርደር አይችሉም። አንዷ ክር በግማሽ ወይም በሙሉ ኖታ ወጣ ወይ ወረድ ብትል፤ ዜማው ስለሚበላሽ ተጨዋቹ መሳሪያውን መቃኘት አሊያም ቅኝት የሚያውቅ ሰው መጥራት አለበት። ልክ እንዲሁ ወንጌላችንም በክርስቶስ መምጣትና ዳግም መምጣት ተወጥሮ የተቃኘ ቃል ነው። ከዚህ ውጥረት የተነሳ መዳናችን፤ ተስፋችን፤ ልጅነታችን፤ በረከታችን፤ አላማችን፤ ቅድስናችን..ወዘተ ልክ እንደ እያንዳንዱ የክራር ክሮች ቅኝት ይዘዋል። ክርስቶስ ከሰማያዊ ሥፍራ ሆኖ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ይህንን ታላቅ የማዳን ዜማ በዓለም ዙሪያ ላሉ ህዝቦችና በአየሩ ላይ ላሉ አለቆች ብዙ ገጽታ ያለውን ጥበብ ይደረድራል። ይህ ግን በጥሩ መልክ የተቃነች ከሆነ ብቻ ነው።
ይህን ሚዛናዊነት ካለመጠበቅ የተነሳ፤ ቤተክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ጽንፈኛ እንቅስቃሴዎች ሲነሱ አይታለች። ይህ ማለት፤ በአንድ እጅ በእውነት ድነናል በሌላ መልኩ ደግሞ ገና ሙሉ በሙሉ መዳናችን አንድ ቀን እንደሚገለጥ በሚዛን አለመያዝ ነው። በአዲስ ኪዳን እነዚህ ሁለት ጽነፈኝነቶች በቅዱሳት መጻሕፍት ለትምህርታችን ተጽፈውልናል። ለምሳሌ ያህል የተሰሎንቄን ቤተክርስቲያንና የቆሮንቶስን ቤተክርስቲያን እንደ ናሙና አድርገን እንውሰድ።
በሽሽት ላይ ያለችው ቤተክርስቲያን! (Under-Realized Soteriology)
ዘራፍ ዘራፍ የምትለዋ ቤተክርስቲያን! (Over-Realized Soteriology)
መስቀልና ዙፋንን ያማጠነች ቤተክርስቲያን! (Realized Soteriology)
“አብረንም እየሠራን የእግዚአብሔርን ጸጋ በከንቱ እንዳትቀበሉ ደግሞ እንለምናለን፤ በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው። አገልግሎታችንም እንዳይነቀፍ በአንዳች ነገር ማሰናከያ ከቶ አንሰጥም። ነገር ግን በሁሉ እንደ እግዚአብሔር አገልጋዮች ራሳችንን እናማጥናለን፤ በብዙ መጽናት፥ በመከራ፥ በችግር፥ በጭንቀት፥ በመገረፍ፥ በወኅኒ፥ በሁከት፥ በድካም፥ እንቅልፍ በማጣት፥ በመጦም፥ በንጽህና፥ በእውቀት፥ በትዕግሥት፥ በቸርነት፥ በመንፈስ ቅዱስ፥ ግብዝነት በሌለው ፍቅር፥ በእውነት ቃል፥ በእግዚአብሔር ኃይል፥ ለቀኝና ለግራ በሚሆን በጽድቅ የጦር ዕቃ፥ በክብርና በውርደት፥ በክፉ ወሬና በመልካም ወሬ ራሳችንን እናማጥናለን፤ አሳቾች ስንባል እውነተኞች ነን፤ ያልታወቁ ስንባል የታወቅን ነን፤ የምንሞት ስንመስል እነሆ ሕያዋን ነን፤ የተቀጣን ስንሆን አንገደልም፤ ኀዘንተኞች ስንሆን ዘወትር ደስ ይለናል፤ ድሆች ስንሆን ብዙዎችን ባለ ጠጎች እናደርጋለን፤ አንዳች የሌለን ስንሆን ሁሉ የእኛ ነው” (2 ቆሮ 6:1–10)
“ነገር ግን የኃይሉ ታላቅነት ከእግዚአብሔር እንጂ ከእኛ እንዳይሆን ይህ መዝገብ በሸክላ ዕቃ ውስጥ አለን፤ በሁሉ እንገፋለን እንጂ አንጨነቅም፤ እናመነታለን እንጂ ተስፋ አንቆርጥም፤ እንሰደዳለን እንጂ አንጣልም፤ እንወድቃለን እንጂ አንጠፋም፤ የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን። የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና። ስለዚህ ሞቱ በእኛ ሕይወቱም በእናንተ ይሠራል። ነገር ግን። አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤ ጌታን ኢየሱስን ያስነሣው እኛን ደግሞ ከኢየሱስ ጋር እንዲያስነሣን ከእናንተም ጋር እንዲያቀርበን እናውቃለንና። በብዙዎች በኩል የተትረፈረፈው ጸጋ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋናን ያበዛ ዘንድ፥ ሁሉ ስለ እናንተ ነውና። ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል። የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ ቀላል የሆነ የጊዜው መከራችን የክብርን የዘላለም ብዛት ከሁሉ መጠን ይልቅ ያደርግልናልና፤ የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው” (2 ቆሮ 4:7–18)
መልዕክቱ ግልጽ ነው፤ መንፈሳዊ ሥጦታ ማለት በክርስቶስ ከመጣው የወንጌል ሙላት አይኖችን ዘወር የሚያደርግ ከሆነ፤ ይህ አዲስ ኪዳን የማያውቀው ስጦታ ነው። እንዲህ አይነት አቋም ቤተክርስቲያን ካልያዘች ወንጌል፡ ከጥቂት ዓመታት በኋላ የማናውቀው ገጽታ ይዞ እናገኛለን። የሞርሞን መስራች ለምን ይመስላችኋል የሳተው? የጆሴፍ ስሚዝ መፎክር “ወደ ጥንታዊቱ የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን እንመለስ” ባይ ነበር። በሞተ ጊዜ ትምሕርተ እግዚአብሄርን፤ ትምሕርተ ክርስቶስን፤ ትምሕርተ ሥነ-ፍጥረትን፤ ትምሕርተ-ቤተክርስቲያንን፤ የቤተሰብ መዋቅር…በሙሉ አዲስ በተቀበለው መገለጦችና ራዕያት ከመበራረዛቸው የተነሳ የሞርሞን ኢየሱስ የኛ ጌታ አይደለም። ተቀበልሁ ብሎ የጻፋቸውን መገለጦች አትመው አሁን እርሱ ታላቅ ነብይ በመባል፤ ጹሑፉም ከመጽሐፍ ቅዱስ በላይ ሥልጣን ያለው ሆኗል። ታድያ እኛስ መንፈሳዊ ሥጦታዎች በምን ረገድ እንደሚሰሩና ምንነታቸውን ካልተረዳን ሞርሞን የወደቁበት ሥህተት የእኛ የማይሆንበት ምን ምክኒያት አለ? እኛስ ሰዎች አይደለንምን? ከወዴት እንደወደቅን ማሰብስ መንፈሳዊነት አይደለምን? አሠራሩ ያው ነውና። በተጨማሪ ከዚህ ቀደም በትምህርቴ ላይ እንዳሰፈርሁት መንፈሳዊ ሥጦታዎች አሁን ክርስቶስ ሃይላትንና ሥልጣናትን ድል አድርጎ በአባቱ ቀኝ ድል አድራጊ ሆኖ መቀመጡን፤ መንግሥቱ በሓይል መመረቋን፤ ማወጂያ መሳሪያ መሆኑን ከኤፌ 4 ላይ አይተናል “ወደ ላይ በወጣ ጊዜ ምርኮን ማረከ ለሰዎችም ስጦታን ሰጠ ይላል። እርሱም አንዳንዶቹን…አድርጎ ሠጠ“
ስለዚህ ትንቢት ተናጋሪው ሲናገር፤ ትንቢቱ በምሪት መስጠት ላይ ይወሰን እንጂ በትንቢት በክርስቶስ የተሰጠውን አስተርዕዮ አይጋፋ። በመንፈስ ቅዱስ የጥበብ ቃል የሚናገር፤ በበሰሉት መካከል የምንናገረው ጥበብ ከሰማይ ዱብ ያለ ሳይሆን አግዚአብሄር አስቀድሞ ለክብራችን የወሰነውን የክርስቶስን ሚስጢር ምን እንደሆነ አስቀድሞ ይማር። በፈውስ ሥጦታ የሚያገለግል ደግሞ አካሉን ያገልግል፤ በመካከላችን በህመም ለሚማቅቁ መለኮታዊ ጉብኝት ያግኙ እንጂ ይህንን ስጦታ አስተማሪ ለመሆን በመሞከር አያዳፍን። ምክኒያቱም አስተማሪዎች ከሁሉ በላይ በልዩ አለንጋ ይገረፋሉና ነው። አስተማሪ ከመሆን በፊት ጥሩ ተማሪ/ ደ/መዝሙር መሆን ምርጫ የለወም። ኢየሱስ ለሦስት ዓመት ተኩል ያሕል ደቀመዛሙርቱን ለሊት-ተቀን አስተምሮ፤ ከዚያም ለ40 ቀናት እያለፈ እያለፈ ከትንሳኤው በኋላ ተገልጦ ይልቅ ካስተማራቸው፤ እኔ ማን ነኝ ታድያ ሳልማር ለማስተማር መሞከር ያለብኝ? ትውስ አይላችሁም ፈሪሳውያን “እነዚህ ሳይማሩ መጽሐፍትን እንዴት አወቁ?”…ጥያቄያቸውንም ራሳቸው በራሳችው ሲመልሱ “ከኢየሱስም ጋር እንደ ነበሩ አወቁአቸው!” ብለዋል። ሳይማሩ ማለታቸው ከፈሪሳውያን ትምህርት ቤት በዶክትሬት ያልተመረቁ ማለታቸው ሲሆን ከኢየሱስ ጋር መሆናቸውን መጦቆማቸው ደግሞ፤ ያ አሳች ብለን የሰቀልነው እርሱ አስተምሯቸዋልና ነው። ምንም እንኳ ከፈሪሳውያን ትምሕርት ቤት ባይመረቁም፤ በክርስቶስ እውነተኛው መምህር እግር ሥር ግን ለሶስት ዓመት ሠልጥነው ተመርቀዋል። በአንጻሩ ደግሞ ቅዱስ ቃሉን ለማስተማር ጸጋ የሰጠን አንዳንዶች ደግሞ ትንቢትና የመገለጥን ቃል ለመናገር ያልተሰጠንን ለመውሰድ ስንሞክር ከቅዱስ ቃሉ እንዳንወጣ በተሰጠን እናገልግል። አሁንም አላማው ሌላውን ለማገልገል እንጂ ታዋቂ ለመሆን አይደለም። ሆኖም ግን ይህ ሁሉ ሥርዓት ይዞ ቅደም ተከተሉን ጠብቆ መሰማራት ይችል ዘንድ በክርስቶስ የመጣው በቅዱሳት መሳሕፍት ጠጠርዞ የቀረበልን የወንጌል አስተርዕዮ በመካከላችን አዛዥ ይሁን!
ስለዚህ እነዚህን ጽንፈኝነቶች አስወግደን በመስቀልና በዙፋን መካከል ቆመን እርስ በርሳችን እየተመካከርን፤ እየተናነጽን፤ እየተገሳሰስን የምንሰብከው ክርስቶስን ይሁን (ቆላ 1፡ 28-29)። በዚህ ዘመን ያለች በቤተክርስቲያን ሊሰበክላት የሚያስፈልገው “ፍጻሜ ገንዘቧ” መሆኑን ነው።፡በርግጥ አይናችን ለዘላለማዊ ርስታችን ታውሯልና ሐዋርያው ለኤፌሶን የጸለየላት ያ ታላቅ ጸሎት ለእኛም ያስፈልገናል “ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው” ብድራታችንን ትኩር ብለን ማየት ተስኖናል። ተስፋችን በሚገለጠው ክብር ላይ ሳይሆን ተስፋችን አሁን እግዚአብሄር በሚያደርገው ጊዜያዊ ትርፍ ነገር ላይ አርፎብናል። በእርግጥ ከላይ የጠቀስኳቸውን ሁሉ ለማስተካከል ታጥቀው የተነሱትን እያንጓጠጥን ‘የሥህተት አስተማሪ’ የሚል ስያሜ ብንሰጣቸውም፤ እውነት ግን በልጆቿዋ ትጸድቃለች። ሆኖም ግን ጴጥሮስስ እንዲህ አላለምን “ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና በመጠን ኖራችሁ፥ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ“ (1 Pe 1:13) ኧረ የቤተክርስቲያን የ2000 ዓመት ቆይታዋንም መመልከት በራሳችን ዓይን ጠቢባን እንዳንሆን ትህትናን ያላብሰናል…ታሪክም ይዳኛልና!
ይህ ሁሉ እንዲህ ከሆነ ታድያ እንዴት እንኑርን?
English Version
“The redemption of man could not be effected by any other, whether by an angel or a man, than the person of God. If anyone other than God were to redeem us from eternal death, the redeemed would be rightly judged to be his servant. Therefore it is not redemption for the redeemed will serve other than God himself (as they do now)”
Therefore, the mission of the Son as described in John 17 includes
- Manifesting the being of the Father to his disciples, thus to us….
“I have manifested your name to the people whom you gave me out of the world. Yours they were, and you gave them to me, and they have kept your word.” (John 17:6)
“I made known to them your name, and I will continue to make it known, that the love with which you have loved me may be in them, and I in them.” (John 17:26)
- Manifesting the life giving and sanctifying Words of the Father from the Son->Apostles->us…
For I have given them the words that you gave me, and they have received them and have come to know in truth that I came from you; and they have believed that you sent me. (John 17:7–8)
Sanctify them in the truth; your word is truth. (John 17:17)
- Manifesting the Glory of both the father and the son by uniting us in Him through the personal presence of the Spirit (the role of the Spirit is reflected in John 14)
that they may all be one, just as you, Father, are in me, and I in you, that they also may be in us, so that the world may believe that you have sent me. The glory that you have given me I have given to them, that they may be one even as we are one, (John 17:21–22)
“I glorified you on earth, having accomplished the work that you gave me to do.”“Father, the hour has come; glorify your Son that the Son may glorify you. ..and now, Father, glorify me in your own presence with the glory that I had with you before the world existed. (John 17:5)
Father, I desire that they also, whom you have given me, may be with me where I am, to see my glory that you have given me because you loved me before the foundation of the world.
01: Salvation is 3D: Three-dimensional
When we were dead in our trespasses, made us alive together with Christ—by grace you have been saved (past)
Since, therefore, we have now been justified by his blood, much more shall we be saved by him from the wrath of God. Romans 5:9(future)
So then let us not sleep, as others do, but let us keep awake and be sober. For those who sleep, sleep at night, and those who get drunk, are drunk at night. But since we belong to the day, let us be sober, having put on the breastplate of faith and love, and for a helmet the hope of salvation. 1 Thessalonians 5:6–8(future)
Blessed be the God and Father of our Lord Jesus Christ! According to his great mercy, he has caused us to be born again to a living hope through the resurrection of Jesus Christ from the dead, to an inheritance that is imperishable, undefiled, and unfading, kept in heaven for you, who by God’s power are being guarded through faith for a salvation ready to be revealed in the last time. 1 Peter 1:3–5 (future)
For the word of the cross is folly to those who are perishing, but to us who are being saved it is the power of God.1 Corinthians 1:18 (Present Continuous) [/column][column]
02: We Are already but not yet fully Saved….
That is why this tension exists. Many of the so called Word-Faith movement preachers and their faithful followers have missed this New Testament tension. They say Jesus has come that we may be fully restored and have life to its fullest, thus prosperity. However, the problem is many read scripture in doses and never in context, thus they don’t seem to catch the fatal error of this movement. Contrarily, the NT stands at a radical middle position, why? It is because when Christ was personal present on earth, he inaugurated both the Kingdom and the new covenant in their real sense but not in their consummated sense. We still yet to experience death, but we have already overcome death (John 5:24). We are not under the power of sin already, but we do still sin and sin is yet to be removed completely from God’s people. The day will come when the bridegroom is taken away, then they will fast. This happened at the ascension of Jesus Christ the Lord of Glory when he was taken up to the right hand of Glory. That is to say, now we are living in this tension in which we are saved in its real sense, because He has already come and finished the work, but, he has yet to return one more time to fully consummate our salvation and render all powers nothing, (i.e. death, sin and Satan).
Law and Grace; Flesh and Spirit
Therefore, my beloved, as you have always obeyed, so now, not only as in my presence but much more in my absence, work out your own salvation with fear and trembling, for it is God who works in you, both to will and to work for his good pleasure. (Philippians 2:12–13)
“But by the grace of God I am what I am, and his grace toward me was not in vain. On the contrary, I worked harder than any of them, though it was not I, but the grace of God that is with me.”
One more:
Your boasting is not good. Do you not know that a little leaven leavens the whole lump? Cleanse out the old leaven that you may be a new lump, as you really are unleavened {new lump}. For Christ, our Passover lamb, has been sacrificed. Let us therefore celebrate the festival, not with the old leaven, the leaven of malice and evil, but with the unleavened bread of sincerity and truth. 1 Corinthians 5:6–8
To be and Yet to be: living in the tension
- We have been saved (Eph 2:8) but we are yet to be saved (Rom. 5:9)
- We have been sanctified (1Cor 6:11) but we are yet to be sanctified (1Thess. 5:23-24)
- We are adopted as sons already (Rom 8:15), but we are yet to be sons (Rom 8:23)
- We have clothed with he new man (Col. 3:9-11), yet we are to be clothed the new man (Eph. 4:21-24)
- We have been redeemed, (Eph. 1:7) but we are yet to be redeemed (Rom 8:23)
Living in light of the End

