Featured_Videos,  Video Posts,  ሕዝቅኤል,  ብሉይ ኪዳን,  የብሉይ ኪዳን ሐቲት

የሕዝቅኤል መጽሐፍ ጥናት: የእግዚአብሔርን ክብር ማወቅ

ዕለቱ July 31, 593 ቅ.ዓ. ነው። ምናልባትም ሕዝቅኤል በእግዚአብሔር ፊት ልቡን ለማፍሰስ ወደ ኮቦር ወንዝ ዳር ሔዶ ሊሆን ይችላል። ይህም ይሆን ይህ የምናውቀው ነገር ቢኖር ሕዝቅኤል ካህን ወይም የካህን ልጅ እንደነበር እና ይህ ቀን ደግሞ የካህኑ 30ኛ የልደት ዓመቱ እንደሆን ነው። የካህኑ የቡዝ ልጅ እንደመሆኑ እድሜ ልኩን ለካህንነት ሲገዘጋጅ እንደ ኖረ መገመት አዳጋች አይደለም።

ሆኖም ግን ከዓምስት ዓመታት በፊት በ597 ቅ.ዓ. ናቡከደነጾር ሁለተኛውን ምርኮ ባደረገ ጊዜ የይሁዳን ንጉሥ ዮአኪንንና ከእርሱ ጋር ወደ 10ሺህ የሚጠጉ የንጉስ ቤተሰቦችንና ሹሟሙንቶችን ተማርከው ወደ ባቢሎንት ተጓዙ። ከነዚህ መካከል የ25 ዓመት ወጣት የሆነው ሕዝቅኤል ነበረበት። ይህ ቀን ኢየሩሳሌም ቢሆን ኖሮ ሰላሳኛውን ዓመት የሚያከብርበት ቀንና ወደ ክህንነት አገልግሎቱ የሚካንበት የሹመት ቀን ይሆን ነበር። አሁን ግን በውርደት ከኢየሩሳሌም መቅደስ ወደ 880 ማይልስ እርቆ ይኖራል። የሚኖረውም በባዕድ ምድር፤ ስደተኞች እንዲሰፍሩ ከተደረጉባቸው ሥፍራዎች አንዱ በሆነውና በኮቦር ወንዝ አቅራቢያ ባለው፤ ቴል አቪቭ በሚባል ሥፍራ ከምርኮኛ ህዝብ ጋር ነው (1:1–3; 3:11, 15)። በምርኮው ዘመን ይሰማ የነበረውን ሰቆቃ ማዳመጥ የሕዝቅኤልን መጽሀፍ በትክክል እንድነረዳና መልክቱን እንድናዳምጥ ያግዘናል። ለምሳሌ ሁለቱን እንመልከት፦

መዝ. 137 “በባቢሎን ወንዞች አጠገብ፣ በዚያ ተቀምጠን ሳለን፣ ጽዮን ትዝ ባለችን ጊዜ አለቀስን። እዚያም በአኻያ ዛፎች ላይ፣ በገናዎቻችንን ሰቀልን። የማረኩን በዚያ እንድንዘምርላቸው ጠየቁን፤ የሚያሠቃዩን የደስታ ዜማ ፈለጉብን፤ ደግሞም፣ “ከጽዮን መዝሙሮች አንዱን ዘምሩልን” አሉን።የእግዚአብሔርን ዝማሬ፣ እንዴት በባዕድ ምድር እንዘምር! ኢየሩሳሌም ሆይ፤ ብረሳሽ፣ ቀኝ እጄ ትክዳኝ። ላስታውስሽ ብቀር፣ ኢየሩሳሌምን የደስታዬ ቍንጮ ባላደርግ፣ ምላሴ ከትናጋዬ ጋር ትጣበቅ”

ሰቆ. 5 “እግዚአብሔር ሆይ፤ በእኛ ላይ የደረሰውን አስብ፤ ውርደታችንን እይ፤ ተመልከትም። ርስታችን ለመጻተኞች፣ ቤቶቻችን ለባዕዳን ዐልፈው ተሰጡ። ወላጅ አልባና አባት የሌላቸው ሆንን፤ እናቶቻችን እንደ መበለቶች ሆኑ። ለምንጠጣው ውሃ መክፈል ነበረብን፤ ዕንጨታችንንም የምናገኘው በግዢ ነበር። የሚያሳድዱን ከተረከዞቻችን ሥር ናቸው፤ ተጨንቀናል ዕረፍትም አጥተናል። እንጀራ እንጠግብ ዘንድ፣ ለአሦርና ለግብፅ እጃችንን ሰጠን። አባቶቻችን ኀጢአት ሠርተው አለፉ፤ እኛም የእነርሱን ቅጣት ተሸከምን። ባሮች ሠልጥነውብናል፤ ከእጃቸው ነጻ የሚያወጣን ማንም የለም። አቤቱ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ለዘላለም ትገዛለህ፤ ዙፋንህ ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል። ስለ ምን ፈጽመህ ትረሳናለህ? ስለምንስ ለረዥም ጊዜ ትተወናለህ? እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ መልሰን፤ እኛም እንመለሳለን፤ ዘመናችንን እንደ ቀድሞው አድስ፤ ፈጽመህ ካልጣልኸን፣ ከመጠን በላይ ካልተቈጣኸን”

የሕዝቅኤል መጽሐፍ ሸክም፡ የእግዚአብሔርን ክብር የማወቅ ግዴታ!

▶️ ስለዚህ ምናልባት ወደ ኮቦር ወንዝ መጥቶ ወደ እግዚአብሔር እሮሮውን ሊያሰማ ሊሆን ይችላል። በዚህ ካህን ልብ ውስጥ ብዙ ጥያቄ ከመኖሩ የተነሳ ኋላ ያህዌህ ወደ አገልግሎት ሲልከው እልሀኛ እንዳይሆን አያሌ ማስጠንቀቂያዎችን ይሰጠዋል።
▶️ ብዙ አንገባጋቢ ጥያቄዎች በዚህ ወጣት ልብ ውስጥ እንዳለ መገመት አዳጋች አይደለም። እነዚህን ጥያቄዎች በሁለት መክፈል እንችላለን።

(1) ያህዌህና ሕዝቡን በጥቅሉ እንዲሁም ሕዝቄልን በግል የተመለከቱ ጥያቄዎች
(2) ያህዌህና ኪዳኑን እንዲሁም ማንነቱን የተመለከቱ ጥያቄዎች።


Every generation is faced with one crucial question that matter the most, a matter of life and death. What is it? It is the question of knowing God. God confronts each generation with Himself and our generation is no different. And yet, not all generation of Christians faces this same question with equal magnitude. There are certain generations who live at the 11th hour of God’s patience. This generation of ours, is in many ways similar to the generation of Ezekiel. When Ezekiel begins to preach among the diaspora in Babylon, at age 30, things were looking really really bad for the people of Judah in every respect. Things weren’t bad because there was famine in the land, or because of their enemies. Things were really bad, because there was no knowledge of Yahweh in Judah. So much so the phrase I will do such and such and they will know that “I AM Yahweh” is repeated more than 65 times in this book.

They were unfaithful to the covenant. But we have to understand this one thing. The trajectory of death didn’t begun with that generation of Ezekiel. Nope! On the one hand we can say Israel has always been hard-hearted (Deut. 29). Though they had seen the awesome work of God through out their journey from Egypt into Jordan, they remained to be rebellious house. As such, seeing God working or being the receiving end of God’s miracles do not necessarily mean conversion. On the other-hand things went irrecoverably bad for Judah exactly 100 years ago, during the days of Manasseh king of Judah. Now, when Ezekiel began his ministry, It was too late for Judah. it really was. The first wave of deportation has already begun 4 years earlier when Nebuchadnezzar stopped by Jerusalem to make Judah a vassal state for Babylon. He captured few of the aristocrats including a young boy by the name: Daniel (Dan. 1፡1-6). Then after 4 years, when Jehoiakim rebelled against Babylon, he stormed into Jerusalem and exiled some 10K people, the nobility and mostly the educated class, including a young man called Ezekiel who was preparing for a priesthood.

Now, would the people listen to Yahweh this time? Well not really. There were many noises. Noises that claim God has spoken to them. Ezekiel’s voice would simply be one of many for them. Yet what Yahweh was about to say, through Ezekiel, was going to determine whether God’s people live or die.

Here is the first video introducing the book of Ezekiel. But, we began thinking through this question of Knowing God.

ሕዝቅኤልና ዘመኑ፡ መግቢያ

የእግዚአብሔር ክብር መልክ አምሳያ፡ አራቱ ፍጡራን፤ መንኮራኩሮችና ጠፈር መሰሉ ዙፋን

“እኔም የእግዚአብሔርን ራእይ አየሁ…በዝናብ ቀን በደመና ውስጥ እንደሚታየው ቀስተ ደመና በዙሪያው ያለው ጸዳል እንዲሁ ነበር። ይህም የእግዚአብሔር ክብር መልክ አምሳያ ነበረ። ባየሁትም ጊዜ በግንባሬ ተደፋሁ፤ የአንድ ተናጋሪን ድምፅ ሰማሁ” (Ezekiel 1:4, 28 (AMHNIV))

ሦስቱ ራዕያት ስለ እግዚአብሔር ዙፋን፡ የእግዚአብሔር ዙፋን ምጡቅ ነው! ሕልው ነው!  ሉዓላዊ ነው! ተዋጊ ነው!

ሕዝ. 1:4-28; ሕዝ. 8፡1-11:25; ሕዝ. 43፡1-12

Leave a Reply

Your email address will not be published.