HEBREWS,  Video Posts,  እብራውያን,  ዕብራውያን,  ዕብራውያን,  የአዲስ ኪዳን ነገረ-መለኮት

የተሾመው መልከ ጼዴቃዊው ካህንና ንጉስ፡ የእብራውያን መጽሐፍ ዳሰሳ

(Class taught for Ethiopian Evangelical Church of Denver)
ከከተማ ወደ ክፍለ ሃገር ስንጓዝ የተለመደ ትዕይንት ትዝ ይለኝ ነበር። በልጅነቴ እስከ አራተኛ ክፍል ድረስ በሆሳዕና ከተማ ነበር ያደኩት። ከዚህ የተነሳ አባቴ የሥራ ዙዉውር አግኝቶ ወደ ናዝሬት ከተማ ከመሔዳችን በፊት፤ በተለይ ደግሞ በአንድ ወቅት ለጥርስ ሕክምና በተደጋጋሚ ወደ አዲስ አበባ ስንጓዝ፤ ትዝ ይለኛል። በልጅ ምናቤ ዱራሜን አልፈን ቡታጅራ ለምሳ እስክናርፍና ደግሞም ከምሳ በኋላ ፍተሻ-ኬላ ድረስ አስክንደርስ፤ በጉጉት እናፍቅ እንደነበርም አስታውሳለሁ። ሆኖም ግን ጉዞ፤ ደግሞም በተለይ በዚያን ጊዜ፤ ከክፍለ ሃገር ወደ ከተማ መጓዝ በጣም አደገኛ እንደነበርም ትዝ ይለኛል። አንዳንድ ግዜም በመንገድ ላይ የተሰበሩ አውቶብሶች፤ የተገለበጡ መኪናዎች፤ ከመንገድ ስተው ገደል የገቡ እንዲሁም የተጋጩ የጭነት መኪናዎችን ስናይ፤ ከመደንገጥ ፋንታ ሁላችንም ያች ጸሃይ ያደረቃትን የአውቶብስ መጋረጃ ከፊታችን ላይ አበስ አድርገን፤ አጮንቁረን ወሬ ለማየት ስንጋፋም ትዝ ይለኛል። መጀምር አንድ ነገር ነው፤ መጨረስ ደግሞ ሌላ ነገር ነው። ጌታንም ስንከተለው እንዲሁ ነው። የዕብራውያን ጸሐፊ ደጋግሞ፤ ይህ የጀመርነው ጉዞ፤ ይህ ወደ ዘመን ፍጻሜ የሚገሰግሰው ትልም፤ ይህ ፍጻሜ ገንዘቡ የሆነ ህዝብ የነፍስ መልሕቅ እንዳለው እንደነገረን ሁሉ፤ ደግሞም ትልቅ የአደጋ ማስጠንቀቂያ በፊታችን እንደተደነቀረም ያስጠነቅቀናል።

▶️ ክፍለ-ጊዜ አንድ (1 of 3)፡ አትመለሱ!

እንደዚህ ዓይነት ታላቅ ሊቀ ካህናት ስላለን፣ እንደዚህ ያለ ጽኑ ምላሽ ልንሰጥ ይጠበቅብናል!

 
“ስለዚህ ከሰማነው ነገር ስተን እንዳንወድቅ፣ ለሰማነው ነገር አብልጠን ልንጠነቀቅ ይገባናል። ምክንያቱም በመላእክት በኩል የተነገረው ቃል ጽኑ ከሆነና ማንኛውም መተላለፍና አለመታዘዝ ተገቢውን ቅጣት ከተቀበለ፣ እኛስ እንዲህ ያለውን ታላቅ ድነት ቸል ብንል እንዴት ልናመልጥ እንችላለን? ይህ ድነት በመጀመሪያ በጌታ ተነገረ፤ ከእርሱ የሰሙትም ለእኛ አረጋገጡልን።” (2:1-4; 3:7–4:13; 5:11–6:20; 10:19–39; 12:14–29).
 

▶️ ክፍለ-ጊዜ ሁለት (2 of 3)፡ በእግዚአብሔር ስለ ተሾመ እና መከራን ስለ ተቀበለ ሊቀ-ካህናት የተገባው ሆኗል (ዕብ 5:1-10)!

ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑ (መለኮታዊ ልጅነቱና በዳዊት ኪዳን ተስፋ መሰረት ንግስናው) ሊቀ-ክህነቱ «ፍቱህ (effective)» እንዲሆን ሲያደርግ፤ ኢየሱስ ፍጹም የሰው ልጅ መሆኑ ደግሞ ሁላችንንም በመወከል በእግዚአብሔር ፊት የሚታይልን ካህን እንዲሆን «ብቁ (qualified] አድርጎታል። እርሱ ሰው በመሆኑ የሁላችንንም በደል ተሸክሞ የሚያስተሰርይ፣ በድካማችን የሚራራልን እንዲሆን አድርጎታል። ከህማማቱ በኋላ፤ ከሙታን ተነስቶ፤ አርጎ በግርማው ቀኝ ሲቀመጥ፤ ወደ ክህነት ቢሮው መግባቱ ነበር። በሰማያት አርጎ የሰው እጅ ወዳልሰራው መቅደስ የገባ ለት “ዛሬ ወለድሁህ” የተባለው ተስፋ ተፈጸመ፤ በመልከጸዴቅም ሥራአት ለዘላለም ካህን ሆኖ ተሾመ። ስለዚህ ይህ የምንናገርለውት “መልከጸዴቃዊ-ንጉስ-ካህን” ይህ የምንናገርለት ሹመት በሁሉ ረገድ የተገባው ሆኗል!! ስለዚህ ወደዚህ ታላቅ ሊቀካህናት ሆኖ ወደተሾመበት ሰማያዊ መቅደስ፤ በደሙ ተረጭተን ደፍረን ሰተት ብለን ወደ እግዚአብሔር መገኘት እንግባ፤ ጸጋን ከፊቱ እንቀበል፤ በፍርሃትና በመንቀጥቅጥ እንታዘዘው። ተስፋችን እና ብድራታችን እውን ነው፤ ምክንያቱም በሁለት መሃላ የጸና ተስፋ ይህም የነፍስ መልህቅ ስላለን ነው። የእግዚአብሔር ቤተሰቦች፤ ይህንን መልህቅ አትልቀቁት! እየተንፏቀቃችሁም ቢሆን ያዙት! ምክኒያቱም ይህ መልህቅ በሹመት የተመረቀው ክህነት እጅ ላይ ተጠምጥሟልና፤ ተስፋችን ሕያው ነው!


“እንዲሁ ክርስቶስ ደግሞ ሊቀ ካህናት ሊሆን ራሱን አላከበረም ነገር ግን። አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወልጄሃለሁ ያለው እርሱ ነው። እንደዚህም በሌላ ስፍራ ደግሞ። አንተ እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ ይላል። እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤ ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤ከተፈጸመም በኋላ በእግዚአብሔር እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ሊቀ ካህናት ተብሎ ስለ ተጠራ፥ ለሚታዘዙለት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት ሆነላቸው።” (ዕብ 5:1-10)

▶️ ክፍለ-ጊዜ ሦስት (3 of 3)፡ “መልከጸዴቃዊ ካህን-ንጉስ” ኢየሱስ ከሌዊ ክህነት ይልቃል (ዕብ 7:1 – 8:6)!

“እንግዲህ ለእኛ የሚያስፈልገን፣ ቅዱስ፣ ነቀፋ የሌለበት፣ ንጹሕ፣ ከኀጢአተኞች የተለየና ከሰማያት በላይ የከበረ እንደዚህ ያለ ሊቀ ካህናት ነው። እርሱም እንደ ሌሎቹ ሊቃነ ካህናት፣ መጀመሪያ ስለ ራሱ ኀጢአት ከዚያም ስለ ሕዝቡ ኀጢአት በየቀኑ መሥዋዕት ማቅረብ አያስፈልገውም፤ ራሱን በሰጠ ጊዜ፣ ስለ ኀጢአታቸው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መሥዋዕት አቅርቦአልና። ሕጉ ደካማ የሆኑትን ሰዎች ሊቃነ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣው መሐላ ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ሾሞአል…እንግዲህ የምንናገረው ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፤”

Leave a Reply

Your email address will not be published.