
የምጋቤ መልእክታት አጠቃላይ ጭብጦች
- ከቀርጤስ ባህል አርነት ያልወጡ የቤተ ክርስቲያን መሪዎችና እውነተኛ የወንጌል ባለ ዐደራነት (ቲቶ)
-
የኤፊሶን የህግ መምህራንና በ እግዚአብሔር ቤት የመኖር ዓላማ (1 ጢሞቴዎስ)
-
የታምኝነት ጥሪና የማፈግፈግ አደጋ (2 ጢሞቴዎስ)
ጢሞቴዎስ
- በእናቱ አይሁዳዊ በአባቱ ደግሞ ግሪክ ነው (ሐዋ 16:1)
- ያልተገረዘ በመሆኑ በአይሁድ ዘንድ ለነበረው ተልእኮ እንቅፋት እንዳይሆን ጳውሎስ ይገርዘዋል
- 1ኛ እና 2ኛ ጢሞቴዎስ በሚጻፉ ሰዓት፣ የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን መሪ ነበር
ቲቶ
- እንዲሁ የጳውሎስ ቅርብ የወንጌል ባልንጀራ ነበር (ቲቶ 1:4)
- ግሪካዊ በመሆኑ፣ አይሁድ ክርስቲያኖች እንዲገረዝ ግድ በማለታቸው፣ ጳውሎስ ይቃወማል
- ጢሞቴዎስና ቲቶ፣ የጳውሎስን የወንጌል ስትራቴጂ ማሳያ ናቸው።
ቲቶ በቀርጤስ
- ቲቶ ከጳውሎስ ጋር አብሮ ከመጓዙ በፊት በቀርጤስ ይኖር ነበር
- ቀርጤስ ከግሪክ ደሴት ሁሉ ስመ ጥር ደሴትና እውቅ ወደብ ነበረች። እንዲሁም የቀርጤስ ንጉሥ በተረት-መሰል ዝናው ታዋቂ ነበር (260-1100 ቅልክ.)
- ከሁሉ በላይ፣ የቀርጤስ ሰዎች በአጭበርባሪነታቸውና በስንፍናቸው የታወቁ እንደ ነበሩ የግሪኩ የ7ኛው ክፍለ ዘመን ጸሐፊ የነበረው ኤፒመነንደስ (Epimenides) ይገልጻቸዋል። ጳውሎስም ይጠቅሰዋል።
በኤፌሶንና በቀርጤስ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ትልቅ ችግር ነበር
- አንዳንድ “የሕግ መምህራን” ነን የሚሉ አማኞችን እያማለሉ “በተረትና በአይሁድ ትውልድ” ምርምር ሰለባ እንዲሆኑ ምክንያት ሆነዋል (1 ጢሞ 1:6–7) ።
- “መምህራን ነን” ቢሉም ግን መምህር ለመሆን የሚያስፈልገውን መመዘኛ ያሟሉም (6-7)
- ይህ ትምህርት የወንጌልን ይዘትና ቅርጽ የሚበርዝ፣ ከሰይጣንና ከስግብግብነት የመነጨ ነው (1 ጢሞ 1:4; 6:3–5; 2 ጢሞ 2:14–16, 23; 3:13; ቲቶ 1:10, 14; 3:9)
ይህ እንግዳ ትምህርትከሚከለክላቸው መካከል
- ትዳርን ይከለክላል፣
- የተወሰኑ ምግቦችን ርኹስ ያደርጋል፣
- “በእውቀት\ግኖሲስ” አንድ ሰው ከምድራዊ ሰውነት መጥቆ፣ ሙታን ትንሳኤ ሊደርስ ይችላል (2 ጢሞ 2:18)
1 ጢሞቴዎስ
- መክፈቻ (1: 1– 2)
- ለጢሞቴዎስ በግል የተሰጠ አደራ፡ በኤፌሶን ስላሉ የሐሰት መምህራን (1: 3– 20)
- ለጉባኤው የተሰጠ መመሪያ፡ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ሊኖር ስለሚገባው አንድነትና ሥርዐት (2: 1– 3: 16)
- ስለ ጸሎት (2: 1– 8)
- በአምልኮ ሰዓት ወንዶችና ሴቶች (2: 9– 15)
- የቤተ ክርስቲያን መሪዎች መመዘኛ (3: 1– 13) ሽማግሌዎች (3: 1– 7) ዲያቆናት(3: 8– 13)
- ለጢሞቴዎስ በግል የተሰጠ ተጨማሪ አደራ (4: 1– 6: 2a)
- ስለ መጨረሻው ዘመን የስህተት መንገድ (4: 1– 5)
- መልካም የክርስቶስ አገልጋይ ስለመሆን (4: 6– 16)
- በቤተኡ ውስጥ ስላሉ ስለተለያዩ የእድሜ ክልል ባሉ ሰዎች እንዴት መያዝ እንዳለባቸው
- የመጨረሻ የወንጌል ዐደራ (6: 2b– 19)
- መዝጊያና ስንብት(6: 20– 21)
2ኛ ጢሞቴዎስ
- መግቢያ/ሠላምታ – [1:1 – 1:5]
- የደብዳቤው ይዘት መግቢያ፡ በግል የቀረበለት ማበረታቻ [1:6 – 18]
- መከራን የመቀበል ጥሪ [1:6 – 14]
- ታማኝ ሆኖ የመገኘት ግዴታ [1:15 – 18]
- የደብዳቤው ይዘት እምብርት፡ እንዴት ማገልገል እንዳለበት [2:1 – 4:8]
- እውነተኛ አገግሎት፤ ወንጌል እና ታማኝነት [2፡1-26]
- ሦስት የአገልግሎት ዘይቤዎች [2:1 – 7]
- ወታደር (2:4)
- ስፖርተኛና (2:5)
- ገበሬ (2:6)
- ወንጌል እና የሚጠይቀው ታማኝነት [2:8 – 13]
- ሦስት ተጨማሪ የአገልግሎት ሚናዎች [2:14 – 26]
- ትጉ ሰራተኛ (2:14–19)
- የተሰናዳ ዕቃ (2:20-21)
- የጌታው አገልጋይ (2:22-26)
- ተጨማሪ ማበረታቻ ቃሎች [3:1 – 4:8]
- የኋለኛው ዘመን ክህደት (3:1 – 9)
- የመጽናት ግዴታ (3:10 – 17)
- የደብዳቤው ይዘት መዝጊያ፡ ቃሉን ስበክ [4:1 – 8]
- የመዝጊያ ስንብት [4:9 – 22]
የምጋቤ መልእክታት አጠቃላይ ነገረ-መለኮታዊ መልእክት
- እውነተኛ አስተምህሮ ትኹረት
- ጤናማ ሊሆን ይገባዋል (1 ጢሞ 1:9-10) – በቁስል የተመታ ጋር ይነጻጸራል (2 ጢሞ 2:17-18)
- እውነት ሊሆን ይገባል (1 ጢሞ 3:15; 2 ጢሞ 2:15)
- ከወንጌል ጋር የሚስማማ
- ከኢየሱስ ትምህርት ጋር የሚስማማ
- ከብሉይ ኪዳን ጋር ሥሙር ነው
- በአደራ የተሰጠ በአደራ የሚጠበቅ ነው
- እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትና ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር (1 ጢሞ 3፡16)
- እውነትን በመልካም ሥራና በመልካም ኑሮ የሚገልጥ (1 ጢሞ 4: 7, 15; 2 ጢሞ 3: 16; ቲቶ 2: 12)
- ቤተ ክርስቲያን (1 ጢሞ 3:15)
- ዘይቤ ፩ – ቤተ/ያን የእውነት አምድና መሰረት
- ዘይቤ ፪ – ቤተ/ያን የእግዚአብሔር ቤተሰብ
- ቤተ/ያን አደረጃጀቷና አገልግሎቷ
- የቃሉ አገልግሎት (እውነት አእማድ)
- የእንክብካቤ አገልግሎት (ቤተሰብ)
- የጸሎት አገልግሎት
- ስለ እግዚአብሔር አብ፣ ስለ ኢየሱስ፣ ስለ መንፈስ ቅዱስ እንዲሁም ስለ ድነት ያስተምራል (God & Salvation)
- ስለ ቤተ ክርስቲያን ተልዕኮና ስለ ዘመን ፍጻሜ (Mission & Last Days)

